የእስራኤል የጦር ካቢኔ አባል ጋንትዝ ከኔታንያሁ የአስቸኳይ ጊዜ መንግስት መልቀቃቸውን ተናገሩ

ሰብስክራይብ
የእስራኤል የጦር ካቢኔ አባል ጋንትዝ ከኔታንያሁ የአስቸኳይ ጊዜ መንግስት መልቀቃቸውን ተናገሩ የእስራኤል የጦር ካቢኔ አባል ቤኒ ጋንትዝ፤ የጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ የአስቸኳይ ጊዜ መንግስት፤ የጋዛ ጦርነትን የመራበትን መንገድ በመቃወም፤ ከካቢኔው በፍቃዳቸው ለመልቀቅ መወሰናቸውን ተናግረዋል፡፡ "ኔታንያሁ ወደ እውነተኛው ድል እንዳንጓዝ መሰናክል ሆኗል። በዚህም ምክንያት እያዘንን ነገር ግን በሙሉ ልብ ሆነን የአስቸኳይ ጊዜ መንግስቱን ለቀናል” ሲሉ እሁድ እለት በቴሌቪዥን በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል። ጋንትዝ፤ ኔታንያሁ የቅድምያ ምርጫ ቀን እንዲቆርጡም ጠይቀዋል። ጋንትዝ፤ ለጋዛ ሰርጥ ወታደራዊ ዘመቻ እስከ ሰኔ 1 ድረስ አዲስ እቅድ ስራ ላይ የማይውል ከሆነ፤ ከአስቸኳይ ጊዜ መንግሥቱ እንደሚለቁ ግንቦት ወር አጋማሽ ውስጥ አስታውቀው ነበር፡፡ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0