ዩክሬን የተሰጣትን ፈቃድ ተጠቅማ የሩስያን ግዛት በአሜሪካ መሳርያዎች ማጥቃት እንደጀመረች የኋይት ሀውስ የደህንነት አማካሪ ተናገሩ

ሰብስክራይብ
ዩክሬን የተሰጣትን ፈቃድ ተጠቅማ የሩስያን ግዛት በአሜሪካ መሳርያዎች ማጥቃት እንደጀመረች የኋይት ሀውስ የደህንነት አማካሪ ተናገሩ "ዩክሬን ድንበር አልፋ እንዳታጠቃ፣ መድፎችን እና የጦር መሳርያ ስፍራዎችን እንዳትመታ መከልከል ምክንያታዊ አይደለም። ለዛም ነው ፕሬዝዳንቱ ፈቀድ የሰጡት። ዩክሬን ይህን ፈቃድ በጦር ግንባሩ ተግባራዊ አድርጋለች" ሲሉ የኋይት ሀውስ የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ ጄክ ሱሊቫን ለሲቢኤስ ኒውስ ተናግረዋል። ቀደም ሲል፤ የዩናይትድ ስቴትስ አስተዳደር የዩክሬን ጦር የተዛወሩለትን የጦር መሳሪያዎች ከካርኮቭ ክልል አቅራቢያ በሚገኙ የሩስያ ግዛት ኢላማዎች ላይ እንዲጠቀም ፍቃድ ሰጥቷል። ነገር ግን፤ ኤ.ቲ.ኤ.ሲ.ኤም.ኤስ (ATACMS) ሚሳኤሎችን እና ሌሎች የረዥም ርቀት መሳሪያዎችን በመጠቀም፤ ድንበር ተሻጋሪ ጥቃቶች ማድረስ ላይ ጥሎት የነበረውን እገዳ አስቀጥሏል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0