ኢራን የሙስሊም ሀገራት ከእስራኤል ጋር ትብብር እንዲያቆሙ ጠየቀች
የኢራን ተጠባባቂ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሊ ባገሪ ከ ሴኤንኤን ቱርክ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ "በእኛ አመለካከት የሙስሊም ሀገራት ሊያደርጉ የሚችሉት ውጤታማው ነገር ከእስራኤል አገዛዝ ጋር ያላቸውን ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ትብብር ማቆም እንዲሁም ከእስራኤል ጋር የሚደረግ ኢምፖርት እና ኤክስፖርትን ማስቀረት ነው" ብለዋል። አክለውም እስራኤል በቀጠናው ለምትፈጥረው አለመረጋጋት፤ ኢራን ኃይሏን ውጤታማ በሆነ መንገድ በመጠቀም እንደምታስቆም አስታውቀዋል።
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ናስር ካናኒ በኤክስ የትስስር ገፀፃቸው ይህን አቋም ያስተጋቡ ሲሆን፤ "በጽዮናውያን እቃዎች እና ኩባንያዎች ላይ ማዕቀብ መጣል ቀላል ነገር ግን በጣም ውጤታማ ነው" ብለዋል።
አክለውም “በመንግሥታት እና የተመድ የፀጥታው ምክር ቤት ዝምታ" ምክንያት፤ ሀገራት እንዲሁም መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ፍልስጤምን የመደገፍ ኃላፊነት አለባቸው” ብለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
https://amh.sputniknews.africa
ኢራን የሙስሊም ሀገራት ከእስራኤል ጋር ትብብር እንዲያቆሙ ጠየቀች
ኢራን የሙስሊም ሀገራት ከእስራኤል ጋር ትብብር እንዲያቆሙ ጠየቀች
Sputnik አፍሪካ
ኢራን የሙስሊም ሀገራት ከእስራኤል ጋር ትብብር እንዲያቆሙ ጠየቀች የኢራን ተጠባባቂ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሊ ባገሪ ከ ሴኤንኤን ቱርክ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ "በእኛ አመለካከት የሙስሊም ሀገራት ሊያደርጉ የሚችሉት ውጤታማው ነገር ከእስራኤል አገዛዝ... 09.06.2024, Sputnik አፍሪካ
2024-06-09T13:27+0300
2024-06-09T13:27+0300
2024-06-11T11:07+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2024
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий