ሩስያ በማእከላዊ አሜሪካ መዋዕለ ንዋይዋን እንድታፈስ የኤል ሳልቫዶር ምክትል ፕሬዝዳንት ጥሪ አቀረቡ

ሰብስክራይብ
ሩስያ በማእከላዊ አሜሪካ መዋዕለ ንዋይዋን እንድታፈስ የኤል ሳልቫዶር ምክትል ፕሬዝዳንት ጥሪ አቀረቡ ሩስያ በኤል ሳልቫዶር እና በአጠቃላይ በማእከላዊ አሜሪካ በመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች ላይ ኢንቨስት እንድታደርግ፤ የኤል ሳልቫዶር ምክትል ፕሬዝዳንት ፌሊክስ ኡሎአ ከስፑትኒክ ጋር ባደረጉት ቃለ መጠይቅ ጥሪ አቅርበዋል። "የክልላችን የልማት አጀንዳ በዓለምአቀፍ ባለሀብቶች ማራኪ [ፕሮጀክት] ፖርትፎሊዮ ላይ የተመሰረተ ነው። በዚህ በኩል ሩስያ በክልሉ ውስጥ ኢንቨስት ለማድረግ የእድል መስኮቶች ሊኖራት ይችላል" ሲሉ ምክትል ፕሬዝዳንቱ በሴንት ፒተርስበርግ ዓለምአቀፍ የኢኮኖሚ ፎረም (SPIEF) ጎን ለጎን ተናግረዋል። የኤል ሳልቫዶር ባለስልጣናት፤ በ180,000 ኪሎ ሜትር (111,000 ማይሎች) "የመንገድ እና የባቡር ሀዲድ፣ አየር ማረፊያ እና ወደብ" ግንባታ፤ ክልሉን የሚያገናኝ የ50 ቢሊዮን ዶላር በላይ እቅድ እንዳላቸው ኡሎአ ገልፀዋል። በሁለተኛው የስልጣን ዘመናቸው የሳልቫዶር ፕሬዝዳንት ናይብ ቡኬሌ፤ በኢኮኖሚ ልማት እና በመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ላይ እንደሚያተኩሩ ኡሎአ ጨምረው ተናግረዋል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0