ኢራን የሩስያ እና የምእራቡ ዓለም ወታደራዊ ፍጥጫን እንደ መፍትሄ አልመለከትም አለች

ሰብስክራይብ
ኢራን የሩስያ እና የምእራቡ ዓለም ወታደራዊ ፍጥጫን እንደ መፍትሄ አልመለከትም አለች የኢራን ተጠባባቂ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሊ ባገሪ፤ በሩስያ እና በምዕራቡ ዓለም መካከል የሚታየውን ወታደራዊ ፍጥጫ ለችግር መፍትሄ አድርጋ እንደማትመለከት ገልፀው፤ ለውይይት ጥሪ አቅርበዋል። አክለውም ሀገራቸው "ለሁለቱም ወገኖች የምትመክረው በፖለቲካ አውድ ውይይትን እንዲጠቀሙ ነው" ብለዋል። በተጨማሪም፤ ኢራን የኒውክሌር መርሃግብሯን የምታከናውነው በአለም አቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ መስፈርቶች መሰረት ነው ያሉት ባገሪ፤ ፕሮግራሙ ሙሉ በሙሉ ህጋዊ ነው እንደሆነ ተናግረዋል። የአይ.ኤ.ኢ.ኤ የገዥዎች ቦርድ የኢራን የኒውክሌር መስፋፋትን የሚያወግዝ ውሳኔ ረቡዕ እለት አጽድቋል። "ኢራን የኒውክሌር መርሐግብሯን የምታካሂደው በአለም አቀፉ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ መስፈርቶች፣ ኒውክሌር ክምችት የመቀነስ ስምምነት እና በራሷ ብሄራዊ ፕሮግራሞች መሰረት ነው። የኢራን የኒውክሌር ፕሮግራም እና እንቅስቃሴ ሙሉ በሙሉ ህጋዊ እና በአለም አቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ቁጥጥር ስር ነው” ሲሉ ባገሪ ተናግረዋል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0