በአፍሪካ የሚገኙ የሩሲያ ኩባንያዎች ሥራቸውን የሚሰሩት ከምዕራባውያን ኩባንያዎች በተለየ መንገድ ነው ሲሉ የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ተናገሩ።

ሰብስክራይብ
በአፍሪካ የሚገኙ የሩሲያ ኩባንያዎች ሥራቸውን የሚሰሩት ከምዕራባውያን ኩባንያዎች በተለየ መንገድ ነው ሲሉ የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ተናገሩ። የሩሲያ ኩባንያዎች በአፍሪካ ሀገራት ልማት ዙሪያ ትኩረት አድርገው የሚሰሩ ናቸው ፣ይህም “ በቅኝ ግዛት ሥር ለነበረች አህጉር በጣም የሚያስፈልግ” ነው። ሲሉ ማሪያ ዛካሮቫ ለስፑትኒክ ተናግረዋል ። ከዚሁ ጋር ተያይዞ አሁንም ቢሆን ምዕራባውያን የአፍሪካ መንግስታትን ፤ በተለይም በተፈጥሮ ሀብት የበለፀጉትን ሃገራት በ “አዲስ ቅኝ ግዛት ”(neo colonial) መርህ የሚገነዘቡበት  አካሄድ እንዳለ ማሪያ ጠቁመዋል። ዲፕሎማቷ በንግግራቸው ትኩረት ያደረጉት፤ በአፍሪካ በማዕድናት ፍለጋ ላይ የተሰማሩ የምዕራባውያን ኩባንያዎች ላይ ሲሆን፤“ያለውን እውነት፣ ለባለሥልጣናቱ፣ ለሕዝብ፣ስለሁኔታው በግልፅ ለመንገር ኃላፊነት አይወስዱም፤ምክንያቱም የአፍሪካን ሀገራት የከርሰ ምድሩ እና ማዕድናቱ ባለቤት አድርገው ስለማይቆጥሩ ነው። "ብለዋል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0