የግንቦትና 28 ቀትር ዋና ዋና የዓለም ዜናዎች

ሰብስክራይብ
የግንቦትና 28 ቀትር ዋና ዋና የዓለም ዜናዎች 🟠 በዪክሬይን ሃይሎች በዛፖሮዝሂ ክልል አንድ መንደር ላይ በተተኮሰ ከባድ መሳሪያ  የአምስት አመት ህጻን ሲሞት ፤11 ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸውን የግዛቲቱ አስተዳደሪ ኢቭጄኒ ባሊትስኪ ተናግረዋል። 🟠 የአየር መከላከያ ቡድኖች በቤልጎሮድ እና በኩርስክ ክልሎች በድምሩ አራት ሰው አልባ አውሮፕላኖች እንዲሁም በቮሮኔዝ ክልል ደግሞ ሌላ አንድ ሰው አልባ አውሮፕላን ትላንት ሌሊት ተኩሰው መምታታቸውን የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል። 🟠የሴንት ፒተርስበርግ አለም አቀፍ የኢኮኖሚ ፎረም ለመጀመር የመጨረሻ ዝግጅት በሴንት ፒተርስበርግ እየተካሄደ ነው። በመድረኩ ተሳታፊዎች እየተሰባሰቡ ነው። 🟠 አሜሪካ የአውሮፓ ህብረት ማዕቀቡን ላልተወሰነ ጊዜ ካራዘመው ፤ የተያዙ የሩሲያ ንብረቶችን በመሸጥ የሚገኘውን ትርፍ ወጪ በማድረግ ለዩክሬን 50 ቢሊዮን ዶላር ብድር ለመስጠት ዝግጁ ነች ፤ሲል ፋይናንሺያል ታይምስ ጽፏል። 🟠 ቀደም ሲል በክራይሚያ የባህር ዳርቻ ታይቶ የነበረው የዩኤስ RQ-4B ግሎባል ሃውክ የተሰኘው የስለላ ሰው አልባ አውሮፕላን አሁንም በ16.7 ኪሎ ሜትር ከፍታ ላይ ከጥቁር ባህር ባሕረ ገብ መሬት አካባቢ፤ ነፃ በሆነው የውሃ አካል ላይ እየዞረ ነው።  ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0