ሶማሊያ የኢትዮጵያ ሠላም አስከባሪ ወታደሮች ሀገሪቱን ለቀው የሚወጡበትን ቀነ ገደብ አስቀመጠች።

ሰብስክራይብ
ሶማሊያ የኢትዮጵያ ሠላም አስከባሪ ወታደሮች ሀገሪቱን ለቀው የሚወጡበትን ቀነ ገደብ አስቀመጠች። የሶማሊያ መንግስት የኢትዮጵያ ወታደሮች እ.አ.አ እስከ ታህሳስ 2024 ሶማሊያን ሙሉ ለሙሉ ለቀው እንዲወጡ ቀነ ገደብ መስጠቱን የሶማሊያ ብሄራዊ ደህንነት አማካሪ ሁሴን ሼክ አሊ ተናግረዋል። እንዲህ ዓይነቱ ውሳኔ ላይ የተደረሰው፤ ኢትዮጵያ የወደብ እና የባህር ሃይል ጦር ሰፈር ለመገንባት፤ ከሶማሊያ ተገንጥላ ራስ ገዝ ሀገር ከሆነችው ከሶማሊላንድ ጋር የመግባቢያ ስምምነት (MoU) መፈረሟን ተከትሎ ነው። ኢትዮጵያ እና ሶማሌላንድ፣ ባለፈው ጥር ወር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል። በስምምነቱ መሰረት ኢትዮጵያ ለሶማሊላንድ የሀገርነት እውቅና ለመስጠት፤ ሱማሌላንድ ደግሞ ለኢትዮጵያ የባህር ሃይል ቤዝ እና የንግድ ወደብ እንዲኖራት የሚያስችል ስምምነት ነው ። ይህንን ስምምነት በሞቃዲሾ መንግስት ዘንድ ህገወጥ እና የሶማሌን ሉዓላዊነት የሚጥስ ነው ማለቷ ይታወሳል። የደህንነት ባለሙያዎች እንደሚሉት የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ጦር ሶማሊያን ለቅቆ እንዲወጣ መወሰኑ ፤ የፀጥታ ሁኔታው ላይ ክፍተት በመፍጠር ሀገሪቱን የበለጠ እንዳትረጋጋ ያደርጋል።  ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0