🪖 ሱሊቫን እና ብሊንከን ዩክሬን ሩስያ ውስጥ እንድታጠቃ ባይደንን አሳምነዋል

ሰብስክራይብ
🪖 ሱሊቫን እና ብሊንከን ዩክሬን ሩስያ ውስጥ እንድታጠቃ ባይደንን አሳምነዋል የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ከብሔራዊ ደህንነት አማካሪያቸው ጃክ ሱሊቫን ጋር ግንቦት 7 ተገናኝተው ተወያይተዋል። በሞላላው ፅህፈት ቤት ሱሊቫን ዩክሬን ካርኮቭ ውስጥ የሩስያን ጥቃቶች ለመከላከል በተለይ ለፀረ-ተኩስ ዓላማዎች፤ እገዳውን በከፊል በማንሳት የአሜሪካ መሳሪያዎችን መጠቀም መቻል እንዳለባት መከራከሩን፤ ፖለቲኮ ምንጮቹን አጣቅሶ ዘግቧል። ባይደን ስምምነታቸውን በመግለፅ ሱሊቫን እና መከላከያ ሚኒስቴሩ የፖሊሲ ለውጡ ላይ እንዲሰሩ ማዘዘቸው ተገልጿል። ውይይቱ በኋይት ሀውስ እየተካሄደ ባለበት ወቅት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንተኒ ብሊንከን፤ ከዩክሬን ባለስልጣናት ጋር ሌላ ዙር ውይይት ለማድረግ ኪዬቭ ገቡ። ብሊንከን ከጉብኝቱ በኋላ፤ ሩስያ የፕሬዝዳንታዊ እገዳውን እየተጠቀመችበት እንደሆነ ለባይደን ገለጻ አድርገዋል። ማንነታቸው እንዳይገለፅ የፈለጉት የጋዜጣው ምንጮች፤ የባይደን ውሳኔ ኪዬቭ ካርኮቭን እንዲሁም በምስራቅ ዩክሬን ውስጥ ሌሎች ወሳኝ ግዛቶችን ታጣለች በሚል ፍራቻ የተገፋፋ ነው ብለዋል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0