ለውጭ ሀገር ብሎገሮች የተዘጋጀ የሚዲያ ትምህርት ተጀመረ - ካሊኒንግራድ የይዘት አዘጋጆችን እያስተናገደች ትገኛለች

Sputnik
በዓለም የወጣቶች ፌስቲቫል ዳይሬክቶሬት እና በወጣቶች ሚዲያ ልማት ማዕከል አዘጋጅነት፤ ከሚያዝያ 27 እስከ 30 ቀን የሚቆይ የውጭ ሀገር "ብሎገሮች" የሚዲያ ትምህርት በካሊኒንግራድ ክልል እየተካሄደ ይገኛል።
ከአብካዚያ፣ አርሜኒያ፣ ቤልጂየም፣ ቦሊቪያ፣ እንግሊዝ፣ ሕንድ፣ ኢንዶኔዥያ፣ ማዳጋስካር እና ከሌሎችም 25 ሀገራት የተውጣጡ 50 ገደማ ብሎገሮች በካሊኒንግራድ ተገኝተዋል። የእነዚህ ብሎገሮች አጠቃላይ ተከታታይ ቁጥር ከ34 ሚሊዮን በላይ ይደርሳል።
​የሚዲያ ትምህርቱ ተሳታፊዎች ሙያዊ ክህሎታቸውን እንዲያሳድጉ፣ ከሩሲያ ባልደረቦቻቸው ጋር ልምድ እንዲለዋወጡ፣ ሀገሪቱን በቀጥታ እንዲያውቁ እና ስለ ሩሲያ የሚስብ ይዘት ለተከታዮቻቸው እንዲያዘጋጁ ታስቦ የተዘጋጀ ነው።
የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ​ማሪያ ዛካሮቫ ባስተላለፉት መልዕክት፣ "አሁን ላይ በዓለም ዙሪያ ማህበረሰቡ በተለያዩ መስመሮች ሲከፋፈል እያየን ነው፤ እናንተ ግን በተቃራኒው ወደ አንድነት እየመጣችሁ ነው። የጋራ መግባቢያ ነጥቦችን እያገኛችሁ ለውይይት ዝግጁ ሆናችኋል። ይህ አመለካከቶችን ለመለዋወጥ እና ዘላቂ ግንኙነቶችን ለመፍጠር ግሩም አጋጣሚ ነው" ሲሉ አፅንዖት ሰጥተዋል።