Sovereignty Sources

የ39ኛው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ አንድምታዎች

Sputnik
''አፍሪካ ቀጣይዋ የልማት፣ ሽግግር እና የኢንዱስትሪ ዘርፍ መሻሻል የፍልሚያ ሥፍራ ናት። አህጉሪቱ ይህን ህልም ለማሳካት በምን ዓይነት መልኩ ቢሆን የተፈጥሮ ኃብቶች ያስፈልጓታል'' ሲሉ የኡጋንዳ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሄነሪ ኦሪየም ኦኬሎ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
ሶስት አንኳር ጉዳዮችን በምንዳስስበት የዛሬው ፕሮግራማችን በክፍል አንድ የ39ኛው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔን መሠረት አድርገን ቁልፍ የትኩረት አቅጣጫዎችን በተመለከተ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች፣ ከኡጋንዳው ሄነሪ ኦሪየም ኦኬሎ፣ ከሪፐብሊክ ኦፍ ጊኒው ሞሪሳንዳ ኩያቴ እና ከቱኒዚያው ሞሃመድ አሊ ናፍቲ ጋር ተወያይተናል። በክፍል ሁለት የኢንዱስትሪ ዘርፍ ማቀላጠፍ እንዲሁም የአፍሪካ ኅብረት 2063 አጀንዳን በሚመለከት የምጣኔ ሐብት ባለሙያውና የፓን አፍሪካ የንግድና ኢንዱስትሪ ምክር ቤት ዋና ዳይሬክተር ክቡር ገና፣ የአፍሬግዚም ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ ፕሬዝዳንት ጂዮርጅ ኢሎምቢ እና አባስ ሚዬዘን ከጋና የንግድና ኢንዱስትሪ ብሔራዊ ምክር ቤት ጋር ሰፋ ያለ ዳሰሳ አድርገናል። የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ ለባህልና ጥበባት ምን ዓይነት ሚና ይጫወት ስንል ከሩዋንዳዊው መምህርና በኢትዮጵያ የስዋህሊ ማኅበረሰብ አባሉ ፊትሶ ሀሩን ጋር ቃኝተነዋል።

ሙሉ መረጃውን ለማግኘት በእንግሊዘኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ Apple PodcastsDeezer Spotify Podcast AddictPocket CastsAfripodsCastBox