“የሀገር-በቀል እውቀት የስነ-ልኬታችን መሳሪያ ነው [...] የአንድ ሰው፣ የአንድ ህዝብ፣ የአንድ ሃገር የጥሩ እና የመጥፎ ነገር መለኪያ ማለት ነው፡፡ ይሄ መጥፎ ነው፣ ይሄ ጥሩ ነው፣ ይሄ ይሻላል፣ ይሄ አይሻልም፣ ይሄ ይበልጣል ይሄ አይበልጥም ብሎ ህዝብ የሚበይንበት፣ የሚለካበት፣ ያሉትን እሴቶች የሚለካበት ነው፡፡ እሱ የለህም ማለት መለኪያህን ተነጠቅህ ማለት ነው፡፡ መለኪያህ ካንተ ወጣ ማለት በሌሎች መለኪያ ውስጥ ትገባለህ፡፡” ሲሉ በሀገር-በቀል እውቀት ጥናት እና ምርምር ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት አቶ አብዱልፈታህ አብደላህ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡
በዚህኛው የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት፣ በኢትዮጵያ እና በአፍሪካ የሀገር-በቀል እውቀት በመደበኛው የትምህርት-ሥርዓት ውስጥ ያለመካተቱን ምስጢር በሀገር-በቀል እውቀት ጥናት እና ምርምር ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት አቶ አብዱልፈታህ አብደላህ በሰፊው አብራርተውታል፡፡ በተጭማሪም በምስራቅ አፍሪካ ፖለቲካ ውስጥ ከፍተኛ የመነጋገሪያ ርዕሰ ጉዳይ እየሆነ ስለመጣው የቀይ ባህር ጉዳይ የታሪክ ተመራማሪ ከሆኑት ከፕሮፌሰር አህመድ ዘካሪያ ያደረግነውም ውይይት በዚህ ዝግጅት ውስጥ ተካትቷል፡፡
ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ፡
ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ : Apple Podcasts – Spotify – Deezer – Afripods – Podcast Addict – Pocket Casts – CastBox
ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ፡
ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ : Apple Podcasts – Spotify – Deezer – Afripods – Podcast Addict – Pocket Casts – CastBox