Drum of Changes

ከትናንት እስከ ዛሬ ፡ የዓለምአቀፍ ተቋማት አድሏዊነትና የፍትሐዊነት ጥያቄ ከሊግ ኦፍ ኔሽን እስከ ጸጥታው ም/ቤት

Sputnik

"አፍሪካ እንደገና የተዋቀረ፣ ገለልተኛ፣ ተጠያቂነት የሰፈነበት ዓለም አቀፍ ስረዐት ያስፈልጋታል። የተባበሩት መንግስታት አሁን ባለው አቋም የአፍሪካን ጥቅም የሚያስከብር አይደለም። በእኔ እይታ የተባበሩት መንግስታት፣ በዩናይትድ ስቴትስ የሚጋለብ፣ምዕራባውያን የሚነዱት ፈረስ ነው።" - ሲሉ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ እና አለም አቀፍ ግንኙነት መምህርና ተመራማሪ የሆኑት አቶ ዳዊት መዝገበ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

በዛሬው የድረም ኦቭ ቼንጅስ ጥንቅራችን ፣ በቀዳሚነት አፍሪካ በተባበሩት መንግስታት እና ሌሎች አለም አቀፍ ተቋመት ውስጥ ፍትሃዊ እና እኩል ውክልና ለማግኘት የምታደርገውን ቀጣይነት ያለው ጥረት እንፈትሻለን። ለዚህም በዲላ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ እን አለም አቀፍ ግንኙነት መምህርና ተመራማሪ የሂኑትም አቶ ዳዊት መዝገበን አነጋግረናል። በሁለተኛው ጥንቅራንም ኃይማኖታዊ እና ባህላዊ ትውፊቶችን ጠብቆ ማቆየት ለአፍሪካ፣ ብሎም ኢትዮጵያ እንደ ሩሲያ ካሉ አገራት ጋር ለሚኖራት መልካም ግንኙነት ስለሚኖራቸው ቦታ ደግሞ ሁለተኛው ጥንቅራችን ያስቀኛናል። በዚህ ጉዳይ ያላቸውን ሃሳብ እንዲያጋሩን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የጥናት እና ምርምር ዳይሬክተር የሆኑትን መምህር ዳንኤል ሰይፈሚካኤልን አነጋግረናል።

ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ: