Sovereignty Sources

ያለምንም የውጭ እርዳታ እና ገደብ ፦ ኢትዮጵያን በውስጣዊ አቅሟ መተማመንን ያረጋገጠችበት ግድብ

Sputnik
''የህዳሴ ግድብ መሠራት አንዱ ሞዕራፍ  ነው። ወንዙ ግን የኢትዮጵያ ልብ ውስጥ ከፍተኛ፣ ሚና ያለው የሶሺዮ - ፖለቲካ መገለጫ፣ የኢትዮጵያ ማንነትና ባህል ጋር ከፍተኛ ቁርኝት ያለው ነው - ብለዋል የውጭ ጉዳዮች ኢንስትቲዩት ምክትል ዳይሬክተር የተከበሩ ዶ/ር አብዲ ዘነበ።''
ዶ/ር አረጋዊ በርሄ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ኃላፊ በበኩላቸው፡-
''አባይ፣ በአፍሪካ ትልቁ ግድብን መገደብ ከተቻለ፣ ሌሎች ግድቦችን ለመገንባት የሚያግደን ምንም ነገር የለም።''
የታላቁ የህዳሴ ግድብ ተጠናቆ በይፋ መመረቁን መሠረት አድርገን ከውጭ ዕርዳታ ውጪ በሰፋ የህዝብ ተሳትፎ መሠራቱ ያለው አንድምታና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች በሰፊው እንዳስሳለን። የሶቨርኒቲ ሶርስስ ፕሮግራም አቅራቢው፣ የውጭ ጉዳዮች ኢንስትቲዩት ም/ዳይሬክተር ዶ/ር አብዲ ዘነበ እና የታላቁ ህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ኃላፊ ዶ/ር አረጋዊ በርሄ በተጨማሪም ዶ/ር ኢንጂነር ታምሩ ተሠማ የአርባምንጭ ዩኒቨርስቲ የውሃ ቴክኖሎጂ ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር እና ተስፋዬ ዳኜ ድሪባ፣ በስፔስ ስሳይንስና ጂዮስፓሺያል ተቋም የዲጂታል ኢሜጅ ፕሮሰሲንግ ሊድ ኤክስኪዩቲቭን ጋብዟቸው በጥልቀት አወያይቷቸዋል።

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ Apple PodcastsAfripodsDeezerPocket CastsPodcast AddictSpotify