“የቅኝ ግዛት ሚዲያዎች በአህጉሪቱ ላይ ችግሮችን ይፈጥራሉ። ምክንያቱም ምዕራባዊያን ሚዲያዎች የአፍሪካ መልካም ጎኖችን ሊዘግቡ ስለማይችሉ። አፍሪካን ሁልጊዜ እንደ ጦርነት፣ ርሃብ እና በሽታ መናኸሪያ ብቻ አድርገው ነው የሚስሉት" ሲሉ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የጋዜጠኝነትና ተግባቦት ት/ቤት መምህር ረዳት ፕሮፌሰር መኩሪያ መካሻ ተናግረዋል።
የአፍሪካ የጋዜጠኛነት ትምህርትን ዳግም ማጤን በርካታ ችግሮችን እንደሚፈታ ይታመናል። በዚህም የዘርፉን ጠቀሜታ እና ተፅዕኖ ለማሳደግ እምቅ መፍትሔዎችን የሚያመጣ እንደመሆኑ በዚህ የሶቨርኒቲ ሶርስስ ፕሮግራም አቅራቢው በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የጋዜጠኝነትና ተግባቦት ት/ቤት መምህራን የሆኑት ረዳት ፕሮፌሰር መኩሪያ መካሻን እና ዶ/ር አብዲሳ ዘርዓይን በመጋበዝ ጥልቅ ወይይት አከናውኗል።
ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ Apple Podcasts – Afripods – Deezer – Pocket Casts – Podcast Addict – Spotify