“ከፕሬዝዳንት ትራምፕ ይልቅ ፕሬዝዳንት ፑቲን ያሸነፉ ይመስለኛል። ትራምፕ በድጋሚ ከተመረጡ በኋላ ዩክሬንን በተመለከተ የታዘብነው አንድ ነገር፣ በምዕራባውያን ኃይላትና አጋራት መካከል ትልቅ ክፍፍል ተፈጥሯል። ቀደም ባሉት ጊዜያት በባይደን አስተዳደር ዘመን አውሮፓውያን ከዋሽንግተን የሚወጣውን ማንኛውንም ነገር በጥብቅ ይከታተሉ ነበር። አሁን ግን ግልጽ ተቃውሞ አይተናል። ዜለንስኪ ቢሆን ፕሬዚዳንት ትራምፕን ይቃረናቸዋል። ስለዚህ አንድ ግልጽ የሆነው ነገር በምዕራባውያን አጋራት መካከል መለያየት ያለ ይመስለኛል " ሲሉ ምሁሩና የፖለቲካ ሳይንቲስቱ ዶ/ር አስናቀ ከፋለ ተናግረዋል።
በዚህ የሶቨርኒቲ ሶርስስ ፕሮግራም አቅራቢው ኃያላኑ የዓለም መሪዎች ቭላድሚር ፑቲንና ዶናልድ ትራምፕ በአላሳካ ያደረጉት ውይይትን በስፋት ያስቃኛል።
በመሪዎቹ ጉባዔ የተነሱ አንኳር ጉዳዮች፣ የግንኙነታቸው ፖለቲካዊ አንድምታ፣ ከጉባዔው መነሻነት ወደፊት የሚጠበቁ ጉዳዮችና ሌሎች በርካታ ተያያዥ ሀሳቦችን ለመወያየት ምሁሩና የፖለቲካ ሳይንቲስቱ ዶ/ር አስናቀ ከፍለ፣ የታሪክ ምሁርና የፖለቲካ ተንታኝ እንዲሁም ጉምቱው ዲፕሎማት አምባሳደር ጥሩነህ ዜናን እንዲሁም ሱዳናዊው የዓለም አቀፍ ፖለቲካ ተንታኝ፣ ዲፕሎማትና ጋዜጠኛው መኪ ኤልሞግራቢን ጋብዟቸዋል።
ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ Apple Podcasts – Afripods – Deezer – Pocket Casts – Podcast Addict – Spotify