በዚህ የራይዚንግ ሳዉዝ፣ ሁለት ጉልበታም የሆኑና ቀጣናውን የሚቀርጹ ጉዳዮች ላይ ትኩረት እናደርጋለን፤ ቢትኮይን ማልማት እና የባህል ማንሰራራት፡፡
በክፍል አንድ፡ የቢትኮይን ባለሙያው ቃል ካሳ የኢትዮጵያ እያደገ የመጣዉ የኤሌክትሪክ ኃይል የክሪፕቶ ኢንደስትሪውን እንዴት እየመገበው እንደሆነይናገራል፤ በያዝነው ዓመት ብቻ ዘርፉ ከ200 ሚሊየን ዶላር በላይ ገቢ አስገብቷል፡፡
ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ ዛሬ ለም/ቤት አባላትበሰጡት ማብራሪያ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በቀጣዩ ዓመት ይመረቃል ብለዋል። ይህም ኢትዮጵያ ለምታደርገው የኤሌክትሪክ ኃይል ሉዓላዊነት ወሳኝ እርምጃ ይሆናል። በአፍሪካ ለሚኖራት የዲጂታል ኢኮኖሚ ሚናም ተጨማሪ አቅምን ይሰጣታል፤ እያደገ የመጣውን የቢትኮይን ማልማት ዘርፍም ይጭምራል፡፡
"ኢትዮጵያ ትርፍ ወይም የተረፈ [የኤሌክትሪክ] ሃይል አላት ይባላል […] ስለዚህ የቢትኮይን ማዕድን አልሚዎች ይህን ትርፍ ሃይል መግዛት ይችላሉ። በግምት 3.2 ሳንቲም/ኪሎዋት በሰዓት እየከፈሉ ነው — ከግብር በኋላ እስከ 3.8ሳንቲም ይሆናል።” ሲል ቃል ካሳ ሃሳቡን ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግሯል፡፡
🎨 በክፍል ሁለት፡ ራይዚንግ ሳዉዝ የደቡባ ትብብር ካውንስል ፌስቲቫልን መነሻ አድርጎ፣ የባህል ነጻነትን ስለመቀዳጀት የተለያዩ ሀሳቦችን ራይዚንግ ሳዉዝ በሰፊው ዳስሷል፡፡
የደቡባዊ ትብብር ድርጅት (ኦኤስሲ) ዋና ጸሐፊ ማንሱር ቢን ሙሳላም ስለዚሁ ጉዳይ ሲያነሱ፦
“ድምፃችንን መመለስ አለብን [...] አሳዛኙ ነገር በህዝቦቻችን፣ በአርቲስቶቻችን እና በባህላዊ ተዋንያኖቻችን መካከል እንዴት ድልድይ መገንባት እንዳለብን አለማወቃችን ነው።” ብለዋል፡፡
የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ረዳት ፕሮፌሰር ነብዩ ባዬ በበኩላቸው፦
አርቲስቶች "በሰሜናዊው ዓለም አስተሳሰቦች የሚመራውን የወጣቶቻችንን ምናብ ለማቅናት መትጋት አለባቸው፡፡” በማለት አሳስበዋል፡፡
ስለ ቢትኮይን 'ማይኒንግ'ም ሆነ ስለ ባህል ሉዓላዊነት በጥልቀት ለመረዳት ይህን በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበዉን የራይዚንግ ሳውዝ ፕሮግራም ይከታተሉ!