የቀይ መስቀል እና የቀይ ጨረቃ ንቅናቄ እንዲጀመር ምክንያት የሆነው እ.ኤ.አ ሰኔ 24 ቀን 1859 ፤ በሰሜን ኢጣሊያ ለንግድ ሥራ ሲጓዝ የነበረው አንሪ ዱና በጣሊያን ሶልፈሪኖ የተመለከተው አሰቃቂ እና ደም አፋሳሽ ጦርነት ነበር። ክስተቱ ዓለም አቀፍ የርህራሄ መልክን ፈጥሮ አልፏል።
ዛሬ የሶቨርኒቲ ሶርስስ ዝግጅታችን ይህንኑ ዕለት ሲያስብ ፣ የደጃዝማች ባልቻ የሩሲያ ቀይ መስቀል ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር አንድሬይ ቭላድሚሮቪች ጎንቻሮቭን በእንግድነት ጋብዟቸዋል።
የሩሲያ ቀይ መስቀል በህክምና ትብብር በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ከ10ዐ ዓመታት በላይ የሰብዓዊ ዲፕሎማሲ ድልድይ ሆኖ ቆይቷል።
ዶ/ር አንድሬ ስለዚሁ ሆስፒታል የታሪካዊ ትስስር ህያው ምስክርነት አጽንኦት ሰጥተዋል፦
ሆስፒታሉ የሩሲያ እና ኢትዮጵያ ግንኙነት መሰረት ነው። የቀድሞውን አሻራ ለመጠበቅና ለማሳደግ ከሀገር እስከ [ግለሰብ] ለአጋርነትን በራችን ሁሌም ክፍት ነው ፣ ብለዋል።
ኢትዮጵያ በ2024 የብሪክስ አባል ሀገር መሆኗን ተከትሎም ፣ ለአጋርነቱ አዲስ መነቃቃት ፈጥሮለታል። ዶ/ር አንድሬ የሩሲያ ሰብዓዊ ድጋፍ ለሌሎች ትብብሮችም መሰረት ሆኗል ይላሉ።
እኛ ስለ ፖለቲካ ወይም ኢኮኖሚ አይደለም [እዚህ ያለነው] - ሕክምና እና ለጤና እንክብካቤ እንጂ ፤ ስራችን ግን ለበርካታ ትብብር መንገድ ይከፍታል ፣ ሲሉ ተናግረዋል።
ሙሉ መረጃውን ለማግኘት የሶቨርኒቲ ሶርስስ ፕሮግራምን ይከታተሉ።
ለማድመጥ ዝግጁ ከሆኑ...