''መሪዎችን መግደል፣ ዜጎችን መግደል፣ ሁሉም ነገር እንዳይንቀሳቀሱ ማድረግ ግፍ ነው። እኛ የምንላችሁን ስሙ፣ እኛ ኃያላን ነን፣ ሁሉንም ነገር ማድረግ እንችላለን ነው የሚሉት። ኢራን በቀጥታ የተፈፀመባት ወረራ ነው -'' ሲሉ በራያ ዩኒቨርሲቲ የሰላም፣ ግጭትና ልማት መምህርና ተመራማሪው ዶ/ር አሌክሳንደር ኃይማኖት ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
በክፍል አንድ ሰሞነኛው የኢራን - አሜሪካ - እስራኤል ግጭትን መሠረት አድርገን በውጭ ጣልቃገብነት ስለሚፈጸሙ የመንግስት ለውጥ፣ ብሔራዊ ራስ ገዝ አስተዳደር እንዲሁም አስገዳጅ የፖለቲካ ሽግግርን ከስነምግባር እና ህጋዊ አንድምታዎች አኳያ በራያ ዩኒቨርሲቲ የሰላም፣ ግጭትና ልማት መምህርና ተመራማሪው ዶ/ር አሌክሳንደር ኃይማኖት ጋር ተወያይተናል። በክፍል ሁለት ከሩሲያ - ኢትዮጵያ ንግድ ፎረም መነሻነት በሀገራቱ መካከል ያለ የሁለትዮሽ ንግድ ግንኙነትን ከዋሲሁን ፍቅሬ የኢትዮጵያ ንግድ እና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ፕሮዝዳነት ጽ/ቤት ኃላፊ ጋር ዳሰናል።
ሙሉውን መረጃ ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:
ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ Apple Podcasts –Deezer – Spotify – Podcast Addict – Pocket Casts – Afripods – CastBox