Sovereignty Sources

ኢራንን እንደ ሀገር ያቆማት ''ጠንካራ'' ብሔራዊ ማንነት

Sputnik
''መሪዎችን መግደል፣ ዜጎችን መግደል፣ ሁሉም ነገር እንዳይንቀሳቀሱ ማድረግ ግፍ ነው። እኛ የምንላችሁን ስሙ፣ እኛ ኃያላን ነን፣ ሁሉንም ነገር ማድረግ እንችላለን ነው የሚሉት። ኢራን በቀጥታ የተፈፀመባት ወረራ ነው -'' ሲሉ በራያ ዩኒቨርሲቲ የሰላም፣ ግጭትና ልማት መምህርና ተመራማሪው ዶ/ር አሌክሳንደር ኃይማኖት ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
በክፍል አንድ ሰሞነኛው የኢራን - አሜሪካ - እስራኤል ግጭትን መሠረት አድርገን በውጭ ጣልቃገብነት ስለሚፈጸሙ የመንግስት ለውጥ፣ ብሔራዊ ራስ ገዝ አስተዳደር እንዲሁም አስገዳጅ የፖለቲካ ሽግግርን ከስነምግባር እና ህጋዊ አንድምታዎች አኳያ በራያ ዩኒቨርሲቲ የሰላም፣ ግጭትና ልማት መምህርና ተመራማሪው ዶ/ር አሌክሳንደር ኃይማኖት ጋር ተወያይተናል። በክፍል ሁለት ከሩሲያ - ኢትዮጵያ ንግድ ፎረም መነሻነት በሀገራቱ መካከል ያለ የሁለትዮሽ ንግድ ግንኙነትን ከዋሲሁን ፍቅሬ የኢትዮጵያ ንግድ እና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ፕሮዝዳነት ጽ/ቤት ኃላፊ ጋር ዳሰናል።
ሙሉውን መረጃ ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:
ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ Apple PodcastsDeezer Spotify Podcast AddictPocket CastsAfripodsCastBox