Continental Drift

"ያመለጡ አጋጣሚዎች እና የደቀኑብን ስጋቶች"፦ የመካከለኛው ምስራቅ ቀውስ ለአፍሪካ የምግብ ሉዓላዊነት የመጨረሻው ማስጠንቀቂያ ?

Sputnik
በዓለም አቀፍ ደረጃ እየታየ ያለው አለመረጋጋት—ከአሜሪካ እና ኢራን ፍጥጫ እስከ ቀይ ባሕር የጸጥታ ስጋት በአፍሪካውያን ማዕድ ላይ ቀጥተኛ ተጽዕኖ እያሳደረ ይገኛል። እንዴት ?

"እውነቱን ለመናገር፣ የዓለም ሥርዓት ወዴት እየሄደ እንደሆነ በጥንቃቄ ብንከታተል ኖሮ፣ የኮቪድ-19 ወረርሽኝን እንደ ጥሩ አጋጣሚ ልንጠቀምበት እንችል ነበር።" — ሲሉ አሻግሬ ዘውዱ (ዶ/ር) በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተፈጥሮ ሳይንስ ኮሌጅ የምግብና የሥነ ምግብ ማዕከል ተባባሪ ፕሮፌሰር ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

በዛሬው የኮንቲነንታል ድሪፍት ዝግጅታችን፤ ከመካከለኛው ምስራቅ ቀውስ ተጽዕኖ በመውጣት የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ከሥነ-ምግብ ባለሙያው አሻግሬ ዘውዱ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተናል። በሁለተኛው ክፍል ደግሞ የአፍሪካን መጻኢ ዕድል በመቅረጽ ረገድ ያለውን የወጣቶች ሚና እንቃኛለን። ለዚህም የኢንተርናሽናል ዩዝ ኮኔክት (IYC) ዳይሬክተር ዳንኤል ዚንያማ እና የፓን-አፍሪካኒዝም ተሟጋቿ ኒያሻ አዶር ጋዚምቢ በእንግድነት ቀርበዋል።
ሙሉ መረጃውን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ ፡

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ Apple PodcastsDeezerSpotifyAfripods Pocket CastsPodcast AddictCastBox