The Rising South

ከአፍ መፍቻ ቋንቋ እስከ ፋይናንስ አቅም፦ የአፍሪካ መዋቅራዊ ሽግግር

Sputnik
“የአፍሪካ የዕውቀት ሥርዓቶች አብዛኛውን ጊዜ የሥነ-ምግባር ወጎችን እና የማኅበረሰብ ትውስታዎችን ያካተቱ ነበሩ። እነዚህ ደግሞ በአፍሪካ ወይም በቅኝ ተገዢ አገሮች ላይ በተጫነው በጽሑፍ በሰፈረ ቀጥተኛ ቀኖናዊ (dogmatic) እና ቢሮክራሲያዊ አመክንዮ ሙሉ በሙሉ ተተኩ። […]ስለዚህ፣ ቋንቋ የአስተዳደራዊ ምክንያታዊነት መሣሪያ በመሆን፣ ተለዋዋጭ የነበሩ ማኅበራዊ ሥርዓቶችን ወደ ደረቅ፣ ሕጋዊ እና ቀኖናዊ የፖለቲካ መዋቅሮች ለውጦታል።” ሲሉ በጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ የማህበራዊ ሳይንስ እና ሂውማኒቲስ ኮሌጅ ዲን አስቻለው ታደሰ (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
በዚህኛው የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅታችን፣ በመጀመሪያው ክፍል በጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ የማህበራዊ ሳይንስ እና ሂውማኒቲስ ኮሌጅ ዲን አስቻለው ታደሰ (ዶ/ር) ጋር በመሆን ዓለም አቀፍ የአፍ መፍቻ ቋንቋ ቀንን ስናከብር የቅኝ ግዛት ቋንቋዎች በአፍሪካ የእውቀት ስርዓት እና በማንነት ላይ ያሳረፉትን ዘላቂ ተጽዕኖ እንዳስሳለን። በተጨማሪም ከአፍሪካ ቢዝነስ ፎረም 2026 የተገኙ ጠቃሚ ግንዛቤዎችን— ከክላቨር ጋቴቴ፣ ከዶ/ር ጁማ ሙክዋና፣ ከቤንጃሚን ኤቪታ ኦማ እና ከፋቱ ኪንቴህ ጋር በመሆን—ስለ ፋይናንስ ሉዓላዊነት፣ ስለ አፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና ፣ ስለ ወጣቶች ፈጠራ እና አህጉሪቱ ለኢኮኖሚ ነፃነት ስለምታደርገው ጥረት በክፍል ሁለት ዝግጅታችን ዳስሰነዋል።
ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ ፡

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ :Apple PodcastsSpotifyDeezerAfripodsPodcast AddictPocket CastsCastBox