አዲስ አበባ የ48ኛው የህብረቱን የሥራ አስፈጻሚዎች ም/ቤት ጉባኤ እያስተናገደች ነው፤የመሪዎች ጉባኤም ከቀናት በኋላ ይቀጥላል።]
"የአፍሪካ ሀገራት [...]በራሳቸው ገንዘብ የመገበያየትን ዕድል ሊያስቡበት ይገባል።[...]ሀገራቱ የውስጥ የገንዘብ ምንዛሪ ስትራቴጂ እንዲኖራቸው ከተስማሙና ሁኔታዎችን ካመቻቹ፣ይህ ለሀገራቱ ጠቃሚ ይሆናል።"ሲሉ የሞሪሸስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሪቲሽ ራምፉ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
ጉባኤው አፍሪካ በባለብዙ ወገን አለም ያላት ሚናም ይመከርበታል።
"ዚምባብዌ በባለብዙ ወገን ግንኙነት ታምናለች።[... ]ብሪክስ ሰላምንና የሰው ልጆችን ዕድገት ከሚደግፉ ተቋማት አንዱ እንደመሆኑ፣በሕገ-መንግሥታችን መሰረት እንድንቀላቀለው የምንበረታታው ድርጅት ነው።" ሲሉ የዚምባብዌ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አኖን ሙርዊራ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
በዛሬው የኮንቲነንታል ድሪፍት ዝግጅታችን፣ በጉባኤው እየተሳተፉ የሚገኙ የአፍሪካ ሀገራት ሚኒስትሮችን ያነሷቸውን ሀሳቦች እናጋራችኋለን።በተጨማሪም እ.ኤ.አ የካቲት 11 የሚከበረውን '' ዓለም አቀፍ የሴቶች እና ልጃገረዶች ቀን በሳይንስ''መነሻ አድርገን ከስፔስ ሳይንስ ተመራማሪዋ ፕሮፌሰር ሚርጃና ፖቪክ ጋር ሰለ ሴቶችን ተሳትፎ ተወያይተናል።
ሙሉ መረጃው ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ ፡
ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ Apple Podcasts –Deezer – Spotify – Afripods – Pocket Casts – Podcast Addict – CastBox