"እያንዳንዱ ማህበረሰብ የራሱ የሆነ ጥበብ እና የራሱ የሆኑ ሀብቶች አሉት። በሚያሳዝን ሁኔታ ግን፣ ማህበረሰቦች እነዚህን ጥበቦች፣ ሀብቶች እና መሣሪያዎች በመደበኛው የትምህርት ሥርዓት ውስጥ ምን ያህል አካተውታል የሚለው ጉዳይ፣ በእኛ ላይ ተጽዕኖ ከማሳደሩም በላይ አሁን ላለንበት የልማት ደረጃ የራሱን አስተዋጽኦ ያበረክታል።" ሲሉ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ ጤና ትምህርት ቤት ባለሙያ እና ተመራማሪ የሆኑት ፕሮፌሰር ሚርጊሳ ካባ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡
በዚህኛው የራይዚንግ ሳውዝ ባለ ሁለት ክፍል ዝግጅት፣ በመጀመሪያው ክፍል በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የግብርና ኮሌጅ ዲን ከሆኑት ዘሪሁን ደምረው (ዶ/ር) ጋር በመሆን በካይሮ በተካሄደው የሁለተኛው የሩሲያ–አፍሪካ የሚኒስትሮች ጉባኤ ላይ የግብርና ዘርፍ ትብብርን አስመልክቶ በሰፊው ተወያይተናል፡፡ ሁለተኛው ክፍልም ትኩረታችንን የሀገር በቀል እውቀቶችን በትምህርት እና በጤና ሥርዓቶች ውስጥ ስለማቀናጀት አድርገን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ ጤና ትምህርት ቤት ባለሙያ እና ተመራማሪ ፕሮፌሰር ሚርጊሳ ፣ በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የአንኮበር የዕፅዋት ሕክምና ፕሮጀክት አስተባባሪ ዶ/ር አማረ አያሌው፣ የማህበረሰብ ጤና ባለሙያ እና የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ከፍተኛ አማካሪ ፕሮፌሰር መንገሻ አድማሱ ካባ ትምህርትን ከቅኝ ግዛት አስተሳሰብ ነፃ ማውጣት፣ የሀገር በቀል ሕክምናን ሚና ተያያዥ ነጥቦች ላይ ሀሳባቸውን አካፍለውናል፡፡
ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:
ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ : Apple Podcasts – Spotify – Deezer – Afripods – Podcast Addict – Pocket Casts – CastBox
ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:
ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ : Apple Podcasts – Spotify – Deezer – Afripods – Podcast Addict – Pocket Casts – CastBox