Sovereignty Sources

የኢትዮጵያ የህክምና ቁሳቁሶችን የማምረት ጅምር፡ ለህክምና ሉዓላዊነት

Sputnik

''ከሩሲያ ኩባንያዎች ጋር በቅርበት እየሰራን እንገኛለን። በአሁኑ ሰዓት ከአራቱ ድርጅቶች ጋር ስምምነት ተፈራርመናል። ገበያው የሚሆነው ኢትዮጵያ ላይ ብቻ ሳይሆን በመላ አፍሪካም ጭምር ነው፡፡'' ሲሉ የቅጥራን ማኒፋክቸሪኒንግ የሜዲካል ኢኪዩፕመንት ትሬዲንግ ባለቤትና ምክትል ሥራ አስኪያጅ ተሾመ በየነ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

በዛሬው የሶቨርኒቲ ሶርስ ፕሮግራም አቅራቢው የሜዲካል ሉዓላዊነት፣ የጤና ዘርፍ ትራንስፎርሜሽን እና አህጉራዊ ተፅዕኖ ጉዳይ ላይ ለመወያየት የቅጥራን ማኒፋክቸሪኒንግ የሜዲካል ኢኪዩፕመንት ትሬዲንግ ባለቤትና ምክትል ስራ አስኪያጅ ተሾመ በየነ ጋብዟቸዋል። በአዲስ አበባ ከተማ የሚስተዋለውን የተሽከርካሪ ጭስ ልቀትንና ተግባራዊ ይደረጋል የተባለውን የተሽከርካሪ ጭስ ልቀት መስፈርትን በተመለከተ ከአውቶሞቲቭ ባለሙያው ፋሲል አስራት ጋር ያደረግነው ቆይታ ሌላኛው የፕሮግራሙ አካል ነው።

ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ: