The Rising South

''የዘመኑ አድዋ'' ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብና የአፍሪካ ሚናና ቦታ በባለብዙ-ዋልታ ዓለም ውስጥ

Sputnik
“የህዳሴው ግድብ፣ እንደ አድዋ ድል ሁሉ፣ አፍሪካውያን "እኛ ማድረግ አንችልም" ወይም "ያለ ድጋፍ መቆም አንችልም" ከሚለው አስተሳሰብ ወጥተው የኢኮኖሚና የፖሊሲ ነፃነታቸውን የሚያረጋግጡበት ትልቅ ክስተት ነው።” ክቡር አቶ መላኩ አለበል
በዚህ የራይዚንግ ሳውዝ ልዩ ዝግጅት፣ የአፍሪካ የፈጠራ፣ የመቋቋም አቅም እና የትጋት ምልክት የሆነውን የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ምረቃን በስፍራው ከተገኙ እንግዶች ጋር በጉባ ተገኝተን ታሪካዊ ክስተቱን እንቃኛለን። ኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል፣ ቀድሞ የዉሃ እና ኢነርጂ አምባሳደር አለማየሁ ተገኑ እና ዶ/ር ያዕቆብ አርሳኖ ግድቡ በኢትዮጵያ የወደፊት እጣ ፈንታ፣ በዲፕሎማሲ እና በክልላዊ ትስስር ላይ ስላለው ተጽእኖ ከግድቡ ግርጌ ሆነው የተለያዩ ሀሳቦችን ሰጥተውናል። ከዚያም፣ በአፋጣኝ በሚለዋወጠው ባለብዙ-ዋልታ ዓለም ውስጥ አፍሪካ የሚያጋጥሟትን ዕድሎች እና ተግዳሮቶች የሚፈትሹትን የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲው ዶ/ር ዳዊት ቢያዝን ጋር ውይይት አድርገናል።
ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ AfripodsDeezerPocket CastsPodcast AddictSpotify