"ቅኝ ገዢዎች ጥለውት የሄዱት ውርሶች አሁንም እንዳሉ አምናለሁ። አሁን ለንግድ እና ለምግብነት የሚውሉ ሰብሎችን ሚዛን ለማስጠበቅ እየሞከርን ነው።" አቡበከር ኪያሪ፣ የናይጄሪያ የግብርና እና ምግብ ዋስትና ሚኒስትር
ለዚህ አይነቱ ለውጥ ሀገር በቀል እውቀቶችን መጠቀምም የግድ ይላል።
"ወደ ሀገር በቀል እውቀት መመለስ አለብን፣ ምክንያቱም የአየር ንብረት ለውጥን እንድንቋቋም፣ የምግብ ዋስትናን እንድናጠናክር እና ለሚመጣው ትውልድ እውቀትን ለማስተላለፍ የሚረዳ ብዙ እውቀት እየጠፋ ነው።" ዊሊስ ኦቺንግ፣ የኬንያ የገጠር ማጠናከሪያና የግብርና ትራንስፎርሜሽን ለዘላቂነት ማዕከል (ክሪየትስ ኢንተርናሽናል) ዋና ዳይሬክተር
ይህ የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት፣ በአዲስ አበባ የተካሄደው የተባበሩት መንግስታት የምግብ ስርዓት ጉባኤ 2025 መነሻዉ አድርጓል። አፍሪካ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የምታደርገውን ጉዞም ይመረምራል። የጉባኤው ተሳታፊ ባለሙያዎችም አህጉሪቱ ከውጭ በሚገቡ ምርቶች ላይ ስላላት ጥገኝነት፣ ራስን ለመቻል እንቅፋት ስለሆኑባት መዋቅራዊ ችግሮች እና ሌሎች ጉዳዮች ላይ ቆይታ አድርገዋል።