"ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ የብዝሃ ህይወት ምንጭ ከሆኑ ሀገራት መካከል አንዷ ነች። ለዚህም ከ125 ሜትር የባህር ወለል በታች፣ ዳሎል እስከ ከፍተኛው የተራራ ጫፍ ወይም 4620 ሜትር የሚረዝመው ራስ ዳሽን ተራራ በአብነት ይጠቀሳሉ። በደን ብዝሃ ህይወት ረገድ በርካታ የዱር እንስሳት፣ እፅዋት፣ አዕዋፋት እና ሌሎቹ ሀገሪቷን ልዩ እንድትሆን አድርገዋታል።”
በዚህ የሶቨርኒቲ ሶርስስ ፕሮግራም አቅራቢው የዱር እንስሳትን እና ቱሪዝምን የሚደግፍ የኢትዮጵያ ከፍተኛ የብዝሃ ህይወት እና አረንጓዴ እድገት እንዲሁም ተያያዥ ጉዳዮች ለመወያየት የብዝሃ ህይወትና አካባቢ ጥበቃ አማካሪው ስሜነህ አድማሱን ጋብዟቸዋል።
ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ Apple Podcasts – Afripods – Deezer – Pocket Casts – Podcast Addict – Spotify