“አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነቱ ትልቅ ዕድል አለው። በ2045 የአፍሪካን ንግድ በ45 በመቶ ገደማ ማለትም በ275.7 ቢሊዮን ዶላር ይጨምራል […] እንዲሁም የአፍሪካ አገሮች የግብርና ምርቶችን ወደ ውጭ የኢንዱስትሪ ምርቶች እንዲልኩ ይረዳቸዋል።”
በዚህ የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት በኢትዮጵያ ፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ተመራማሪ ከሆኑት አበበ አምባቸዉ (ዶ/ር) ጋር በመሆን የታሪፍ ቅነሳን በማስወገድ እና የኢንዱስትሪ እድገትን በማበረታታት የአህጉሪቱን የንግድና ኢኮኖሚያዊ ውህደትን ስለሚያሳድገው የዓለም ትልቁ የነፃ ንግድ ቀጠና ስምምነት ላይ ተወያይተናል ፤ የኢትዮጵያን የመጨረሻ ምዕራፍ ዝግጅቶችንም ዳስሰል።