The Rising South

የአፍሪካ ልማት ባንክ አዲሱ ፕሬዝዳንት እና የአፍሪካ ማንነትን ለመጠበቅ የሚደረገው ትግል

Sputnik
ዛሬ በጎርጎሮሳዊያኑ ሐምሌ 15፣ በዓለም የወጣቶች ክህሎት ቀን ፣ የአፍሪካ ልማት ባንክ እያንዳንዱ ኢንቨስትመንት የወጣቶችን የስራ እድል ፈጠራን ለማስቀደም ያስችላል የሚለውን ስርዓት አስተዋውቋል።
ባንኩ የ10 ዓመት ስትራቴጂ አካል የሆነ የወጣቶች የስራና ክህሎት 'ማርከር' ስርዓትን ከዓለም የስራ ድርጅት ጋር በመሆን ይፋ አድርጓል። ይህ ውሳኔ የመጣው ባንኩ ሲዲ ኡልድ ታህን (ዶ/ር) ዘጠነኛ ፕሬዝዳንት አድርጎ ከመረጠ በኋላ የሆነ ነው።
እንዲህ ያሉ የአፍረካ ለውጦችን ዕውን ለማድረግ የአፍሪካ ማንነትን መጠበቅና የወደፊት ትውልድን ማብቃት አስቸኳይ እንደሆነ ባለሙያዎች አጽንኦት ሰጥተዉ ይናገራሉ።

"ዛሬ ከአሜሪካ ቅነሳ አለን፣ እና በሚቀጥለው ዓመት ወይም በሚቀጥሉት ዓመታት ከምዕራባውያን አገሮች ሙሉ በሙሉ ቅነሳ ሊኖርብን ይችላል፣ ምክንያቱም አብዛኛዎቹ የአፍሪካ አገሮች ወደ ብሪክስ ለመቀላቀል እንቅስቃሴ እያደረጉ ነው፣ [...] የአፍሪካ ልማት ባንክ ከውስጥ ምንጮች ዘላቂ የሆነ ምንጭ ሊፈልግ ይገባል፡፡" ሲሉ ፈንታሁን ባይሌ (ዶ/ር) ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ ለራይዚንግ ሳውዝ ተናግረዋል።

በተጨማሪም ምዕራባውያን ወይም አፍሪካዊ ያልሆኑ ምንጮች የሚመጡ የገንዘብ ድጋፍ የአንድን ሀገር ሉዓላዊነት ሊጎዳ ወይም ለጋሽ ለሚፈልገው ነገር እንዲያመች የሚያደርጉ ቅድመ ሁኔታዎችን ሊይዝ ይችላል ብለዋል።
እንዲሁም በዚህ ፕሮግራም ላይ፦
ፕሮፌሰር አለማየሁ ተክለማርያም፣ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ የአፍሪካ ማንነትን ለመጠበቅ እና ቀጣዩን ትውልድ በትምህርት እና በባህል ለማብቃት በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ያብራራሉ።
የአፍሪካን የፋይናንስ የወደፊት ዕጣ እና ማንነትን ስለመጠበቅ የበለጠ ለማወቅ ይህንን በእንግሊዘኛ ቋንቋ የቀረበውን ባለ ሁለት ክፍል የራይዚንግ ሳውዝ ፕሮግራም ይከታተሉ።
ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ AfripodsDeezerPocket CastsPodcast AddictSpotify