በአፍሪካ በተንቀሳቃሽ ስልኮችና መሠል መሣሪያዎች ላይ በሚጫኑ መተግበሪያዎች አማካኝነት የሚሳለጡ የንግግድ ልውውጦች በፍጥነት እየጎለበቱ ነው።
የሶቨርኒቲ ሶርስስ ፕሮግራም በዛሬው መርሃ ግብሩ በኤክትሮኒክ መር ገበያ ስለሚሳለጡ የፋይናንስ ልውውጦች፣ በብሪክስ ሀገራት መካከል ስላለ መልካም ዕድልና የአፍሪካ ሀገራት ትብብር እንዲሁም ሌሎች ተያያዥ ሀሳቦች በጥልቀት ለመወያየት ማርቆስ ጥላሁን፣ የኤሌክትሮኒክ ግብይት ባለሙያ እና ፕሮሞተርን ጋብዟቸዋል።
በአፍሪካ አህጉር የኤሌክትሮኒክ ግብይት እድገትን በተመለከተ ማርቆስ ጥላሁን ሲናገሩ፦
"በአፍሪካ አህጉር የኢ-ኮሜርስ ባለፉት አስርት ዓመታት በርካታ አስደናቂ እድገትን አስመዝግቧል። ይህም በአብዛኛው የበይነ መረብ ግንኙነት መጨመር፣ የሞባይል ተኮር የፋይናንስ እንቅስቃሴ እና እያደገ በመጣው የወጣቶች የቴክኖሎጂ እውቀት የበለጠ ይጠናከራል። ለአብነትም በአህጉሪቱ እንደ ኢትዮጵያ፣ ኬንያ፣ ናይጄሪያ እና ደቡብ አፍሪካ ያሉ አገሮች የዘርፉ ግንባር ቀደም ተሳታፊ ሆነዋል - ሲሉ ተናግረዋል።''
በብሪክስ ሀገራት እና በአፍሪካ ላለው የዲጂታል ግብይት መስፋፋት ተንቀሳቃሽ ስልኮች አይነተኛ ቶችሚናን እየተጫወቱ ነው።
"በብሪክስ አገራት እና የአፍሪካ የዲጂታል የግብይት ሂደትን የሚያፋጥኑ በርካታ ምክንያቶች ይጠቀሳሉ። እንደማስበው በዋናነት የሞባይል- መር አቀራረብ ዋነኛውና አስፈላጊ ነገር ነው፣ በተለይም በአፍሪካ፣ ልዩ የሞባይል - ተኮር አቀራረብ ነው። ይህ ዋነኛ ዘዋሪ ጉዳይ ነው። የሞባይል ስልክ አጠቃቀም ሰፊ ነው"፣ ሲሉ ማርቆስ ጥላሁን ተናግረዋል
የ ኤሌክትሮኒክ ግብይት ስርዓት የአፍሪካ አገራት በአህጉር ደረጃ እንዲሁም በብሪክስ የትብብር ማቀፍ ሥር ስር ነቀል ለውጥ እንደሚያመጣ ይታመናል።
በቆይታችን - በኤክትሮኒክ መር የሚሳለጡ የገበያ ልውውጦች፣ በብሪክስ ሀገራት መካከል ስላለ መልካም ዕድልና የአፍሪካ ሀገራት የሚያገኟቸው ተሞክሮዎች የለውጥ ጎዳና ላይ ላለችው አህጉር ምን ትሩፋት ያመጡላታል? የሚሉ አንኳር ጥያቄዎችን አንስተናል።