ኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የብሔራዊ አንድነት መንግሥት ለማቋቋም ውይይት ልትጀምር ነው

ኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የብሔራዊ አንድነት መንግሥት ለማቋቋም ውይይት ልትጀምር ነው የፕሬዝዳንቱ አማካሪ እንዳስታወቁት ውይይቱ መጋቢት 15 ቀን ይጀመራል። ውይይቱ የሚከተሉትን አካላት ያካትታል፦ 🟠 ገዢው የፓርላማ ጥምረት፤ ዩኒየን ሳክሬ፣🟠 በፓርላማ እና ከፓርላማ ውጭ ያሉ የተቃዋሚ ፓርቲዎች፣🟠 የሲቪል ማሕበረሰቦች እና የቀድሞ ፕሬዝዳንታዊ እጩዎች እና ታዋቂ ግለሰቦች። ምክክሩ በሚከተሉት ቁልፍ መርሆች ላይ የተመሠረተ ይሆናል ፡- 🟠 የሕገ-መንግሥቱ የበላይነት፣🟠 ብሔራዊ አንድነት፣🟠 የሀገሪቱ ድንበር አይደፈሬነት፣🟠 ብሔራዊ ሉዓላዊነት፣🟠 ለተቋማት ክብር መስጠት፣🟠 ሁሉን አቀፍ እና አሳታፊ አስተዳደር። ሬዲዮ ኦካፒ እንደዘገበው ሂደቱ ከሁለት ሳምንት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃል። የኮንጎ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ፌሊክስ ቺሸኬዲ በየካቲት ወር መጨረሻ በተለይም በሀገሪቱ ምስራቅ ክፍል ያለውን የውጭ ስጋት ለመቅረፍ የውስጥ ልዩነቶችን ማጥፋት አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል። በተጨማሪም የብሔራዊ አንድነት መንግሥት መቋቋሙን አስታውቀው ነበር።በእንግሊዘኛ ያንብቡ@sputnik_ethiopia መተግበሪያ | X ላይ ይከተሉን
Sputnik
ኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የብሔራዊ አንድነት መንግሥት ለማቋቋም ውይይት ልትጀምር ነው የፕሬዝዳንቱ አማካሪ እንዳስታወቁት ውይይቱ መጋቢት 15 ቀን ይጀመራል። ውይይቱ የሚከተሉትን አካላት ያካትታል፦ 🟠 ገዢው የፓርላማ ጥምረት፤ ዩኒየን ሳክሬ፣🟠 በፓርላማ እና ከፓርላማ ውጭ ያሉ የተቃዋሚ ፓርቲዎች፣🟠 የሲቪል ማሕበረሰቦች እና የቀድሞ ፕሬዝዳንታዊ እጩዎች እና ታዋቂ ግለሰቦች። ምክክሩ በሚከተሉት ቁልፍ መርሆች ላይ የተመሠረተ ይሆናል ፡- 🟠 የሕገ-መንግሥቱ የበላይነት፣🟠 ብሔራዊ አንድነት፣🟠 የሀገሪቱ ድንበር አይደፈሬነት፣🟠 ብሔራዊ ሉዓላዊነት፣🟠 ለተቋማት ክብር መስጠት፣🟠 ሁሉን አቀፍ እና አሳታፊ አስተዳደር። ሬዲዮ ኦካፒ እንደዘገበው ሂደቱ ከሁለት ሳምንት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃል። የኮንጎ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ፌሊክስ ቺሸኬዲ በየካቲት ወር መጨረሻ በተለይም በሀገሪቱ ምስራቅ ክፍል ያለውን የውጭ ስጋት ለመቅረፍ የውስጥ ልዩነቶችን ማጥፋት አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል። በተጨማሪም የብሔራዊ አንድነት መንግሥት መቋቋሙን አስታውቀው ነበር።በእንግሊዘኛ ያንብቡ@sputnik_ethiopia መተግበሪያ | X ላይ ይከተሉን