ኢጋድ የሱዳን የሰላም ሂደት በሱዳናውያን ሊመራ ይገባል አለ

ኢጋድ የሱዳን የሰላም ሂደት በሱዳናውያን ሊመራ ይገባል አለበሱዳን የሽምግልና ጥረቶችን የሚደግፍ እና እውነተኛ መፍትሔ ለማምጣት ያለመ የኢጋድ ልዩ መልዕክተኞች መድረክ በዛሬው እለት በአዲስ አበባ ተካሂዷል።በመድረኩ ላይ የተገኙት የኢጋድ ዋና ፀሃፊ ወርቅነህ ገበየሁ ሁሉም የሰላም ተዋናዮች የዲፕሎማሲያዊ ጥረቶቻቸውን ሊያስተባብሩ ይገባል ሲሉ በኤክስ የትስስር ገጻቸው ላይ ተናግረዋል፡፡ኢጋድ ከአፍሪካ ሕብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እና ሌሎች ዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር በመተባበር፤ በሱዳናውያን ለሚመራ የሰላም ሂደት ቁርጠኛ እንደሆነም ዋና ፀሃፊው ጨምረው ገልጸዋል፡፡@sputnik_ethiopia መተግበሪያ | X ላይ ይከተሉን
Sputnik
ኢጋድ የሱዳን የሰላም ሂደት በሱዳናውያን ሊመራ ይገባል አለበሱዳን የሽምግልና ጥረቶችን የሚደግፍ እና እውነተኛ መፍትሔ ለማምጣት ያለመ የኢጋድ ልዩ መልዕክተኞች መድረክ በዛሬው እለት በአዲስ አበባ ተካሂዷል።በመድረኩ ላይ የተገኙት የኢጋድ ዋና ፀሃፊ ወርቅነህ ገበየሁ ሁሉም የሰላም ተዋናዮች የዲፕሎማሲያዊ ጥረቶቻቸውን ሊያስተባብሩ ይገባል ሲሉ በኤክስ የትስስር ገጻቸው ላይ ተናግረዋል፡፡ኢጋድ ከአፍሪካ ሕብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እና ሌሎች ዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር በመተባበር፤ በሱዳናውያን ለሚመራ የሰላም ሂደት ቁርጠኛ እንደሆነም ዋና ፀሃፊው ጨምረው ገልጸዋል፡፡@sputnik_ethiopia መተግበሪያ | X ላይ ይከተሉን