የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና የአፍሪካ ልማት ባንክ ቢሾፍቱ አቅራቢያ በሚገነባው ግዙፍ አየር ማረፊያ ዙርያ በጋራ ለመሥራት የሚያስችላቸውን የፍላጎት መግለጫ ስምምነት ሰነድ ተፈራርሙ ስምምነቱን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው እና የአፍሪካ ልማት ባንክ የቀጣናዊ ልማት፣ ትስስር እና ስትራቴጂ ምክትል ፕሬዝዳንት ኔና ንዋቡፎ በትናንትናው እለት ተፈራርመዋል። 7.8 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ወጪ ይደረግበታል ተብሎ የሚገመተው ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት፤ እ.አ.አ በ2040 የአየር መንገዱን ዓመታዊ መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ከ17 ሚሊዮን ወደ 60 ሚሊዮን ያሳድጋል ተብሎ ይጠበቃል። መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia