ኤርትራ እና የአፍሪካ ልማት ባንክ በአነስተኛ የፀሀይ ኃይል ቋት ፕሮጀክት ዙርያ የ20 ሚሊዮን ዶላር ስምምነት ተፈራረሙ

ኤርትራ እና የአፍሪካ ልማት ባንክ በአነስተኛ የፀሀይ ኃይል ቋት ፕሮጀክት ዙርያ የ20 ሚሊዮን ዶላር ስምምነት ተፈራረሙአዲሱ ስምምነት ባለፈው ዓመት የተፈረመውን የ50 ሚሊዮን ዶላር ፕሮጀክት እንደሚደግፍ እና በደቀምሃሪ ከተማ የፀሀይ ኃይል ማመንጫ ለመገንባት የወጠነ እንደሆነ የኤርትራ የማስታወቂያ ሚኒስትር የማነ ገበረመስቀል ተናግረዋል።ሁለቱ ስምምነቶች ከኤርትራ መንግሥት ብሔራዊ የኃይል አቅምን የማሳደግ የመካከለኛ ጊዜ ስትራቴጂ ጋር የሚጣጣሙ ናቸው ተብሏል። እያንዳንዳቸው 30 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያላቸው 12 የሞዱላር ኢነርጂ ማመንጫዎችን ለመትከል የታቀደ ሲሆን ይህም ነባሩን የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም በከፍተኛ ደረጃ ያሳድገዋል ተብሎ ይጠበቃል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
Sputnik
ኤርትራ እና የአፍሪካ ልማት ባንክ በአነስተኛ የፀሀይ ኃይል ቋት ፕሮጀክት ዙርያ የ20 ሚሊዮን ዶላር ስምምነት ተፈራረሙአዲሱ ስምምነት ባለፈው ዓመት የተፈረመውን የ50 ሚሊዮን ዶላር ፕሮጀክት እንደሚደግፍ እና በደቀምሃሪ ከተማ የፀሀይ ኃይል ማመንጫ ለመገንባት የወጠነ እንደሆነ የኤርትራ የማስታወቂያ ሚኒስትር የማነ ገበረመስቀል ተናግረዋል።ሁለቱ ስምምነቶች ከኤርትራ መንግሥት ብሔራዊ የኃይል አቅምን የማሳደግ የመካከለኛ ጊዜ ስትራቴጂ ጋር የሚጣጣሙ ናቸው ተብሏል። እያንዳንዳቸው 30 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያላቸው 12 የሞዱላር ኢነርጂ ማመንጫዎችን ለመትከል የታቀደ ሲሆን ይህም ነባሩን የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም በከፍተኛ ደረጃ ያሳድገዋል ተብሎ ይጠበቃል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦   APK ፋይል ሊንክ  ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia