ብሪታኒያ አሜሪካን ችላ በማለት ከዩክሬን ጋር መረጃ ለመለዋወጥ የሚያስችል የስለላ ጥምረት ልትፈጥር ነው ተባለ ይህ ሀሳብ አሜሪካ ከኪዬቭ ጋር የምታደርገውን የመረጃ ልውውጥ ካቆመች እና ብሪታንያ እና ሌሎች አጋሮቿ መረጃዋን ወደ ዩክሬን እንዳያስተላልፉ መከልከሏን ተከትሎ የመጣ ነው። ፋይፍ አይስ ኢንቴል አሊያንስ በሚባለው የመረጃ ጥምረት ሥር የሚቋቋመውና ፎር አይስ ተብሎ ይጠራል የተባለው ንዑስ ቡድን፤ ያለ ዩናይትድ ስቴትስ እገዳ መረጃ መለዋወጥ እንደሚያስችል የብሪቲሽ ጋዜጣ ዘገባ አስነብቧል።በእንግሊዘኛ ያንብቡመተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia