የጋና ፕሬዝዳንት በሳህል ሀገራት ጥምረት እና ኢኮዋስ መካከል መተማመን ለመፍጠር ቃል ገቡ ፕሬዝዳንቱ ጆን ማሃማ በማሊ ባማኮ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ በሁለቱ ቡድኖች መካከል “መተማመን እንደሌለ” ገልፀው፤ መተማመኑን ለመመለስ ጥረት እንደሚደረግ አረጋግጠዋል። የማሃማ የማሊ ጉብኝት በጋና እና ማሊ መካከል ያለውን ኢኮኖሚያዊ ግንኙነት እንዲሁም የማሊ ዲያስፖራ ጋና ውስጥ የሚጫወተውን ሚና በማጠናከር ላይ ያተኮረ እንደነበር ታውቋል። በተጨማሪም የሁለቱን ሀገራት የጋራ ትብብር ኮሚሽን ማነቃቃትና ሽብርተኝነትን ለመከላከል የሚደረገውን ጥረት ጨምሮ ቁልፍ የጸጥታ ችግሮችን ለወቅረፍ ያለመ ውይይት ተደርጓል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia