የኢትዮጵያ አየር ኃይል በአል-ሻባብ ዒላማዎች ላይ ጥቃት መፈፀሙን የሶማሊያ መከላከያ ሚኒስትር አረጋገጡ የሀገሪቱ መከላከያ ሚንስትር አብዱልቃድር ሞሃመድ የኢትዮጵያ አየር ኃይል ጥቃት በሶማሊያ ማዕከላዊ ሻበሌ ክልል በሚገኙ የአል-ሻባብ ዒላማዎች ላይ ያነጣጠረ እንደነበር ተናግረዋል። ጥቃቱ ከሶማሊያ መንግሥት ጋር በቅንጅት እንደተካሄደ የመከላከያ ሚኒስትሩ ጨምረው ገልፀዋል። "ሶማሊያ ውስጥ የሚደረግ የትኛውም የአየር ጥቃት ያለ መንግሥት እውቅና አይደረግም" ሲሉ አጽንኦት የሰጡት ሚኒስትሩ፤ በሶማሊያ እና ኢትዮጵያ መካከል ያለው የደህንነት ትብብር እየጨመረ መምጣቱን ጠቁመዋል። ጥቃቱ የኢትዮጵያና ሶማሊያ ጦር አዛዦች በቅርቡ በሞቃዲሾ የደረሱትን ስምምነት ተከትሎ የመጣ ነው። መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia