ሩሲያ በቅርቡ ያቋቋመችው የአፍሪካ ቢሮ የሞስኮ እና አፍሪካ ግኑኝነት እየተጠናከረ እና እየሰፋ መምጣቱን የሚያሳይ እንደሆነ ተገለፀበሞስኮ የኢትዮጵያ አምባሳደር ገነት ተሾመ በሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ትብብር ቢሮ ዳይሬክተር ታትያና ዶቫጋሊንኮ ጋር ተገናኝተው ተወያይተዋል። ሩሲያ ከአፍሪካ ጋር ያላትን ትብብር የሚመለከት ቢሮ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሯ ውስጥ መክፈቷ፤ የሩሲያ እና አፍሪካ ሁለንተናዊ ግንኙነት እያደገ መምጣቱን ያሳያል ሲሉ ዳይሬክተር ታትያና ዶቫጋሊንኮ ተናግርዋል።ቢሮው ከአፍሪካ ሕብረት እና ከክልላዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች እንዲሁም ከአህጉሪቱ ሀገራት ጋር ግንኙነት ለማቀላጠፍና ትብብር ለማሳደግ እንደሚሰራ ዳይሬክተሯ አስታውቀዋል። አምባሳደር ገነት በበኩላቸው ሚኒስቴሩ ዲፓርትመንቱን ለማቋቋም ያሳለፈውን ውሳኔ አድንቀው፤ አዲሱ መዋቅር በሩሲያ ፌዴሬሽን እና አፍሪካ መካከል ያለውን ትብብር እና የጋራ ተጠቃሚነት ያሳድጋል ብለው እንደሚያምኑ ገልጸዋል። መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia