ፕሬዝዳንት ትራምፕ ዩናይትድ ስቴትስ ከዩክሬን ጋር የማዕድን ውል ለመፈራረም "ተቃርባለች" አሉ "እኛ ውድ ማዕድናት እና ነዳጅ...ማግኘት የምንችለውን ሁሉ እየጠየቅን ነው። የሰጠነውን ገንዘባችንን እንመልሳለን። ገንዘባችንን መልሰን እናገኛለን፤ ምክንያቱም ፍትሐዊ አይሆንም። (...) ሆኖም ለስምምነት በጣም ቅርብ ነን ብዬ አስባለሁ፤ ስምምነት ላይ ብንደርስ ነው የሚሻለን፤ ምክንያቱም ሁኔታው ደስ የማይል ነበር" ሲሉ ትራምፕ በዋሽንግተን በተካሄደ የወግ አጥባቂዎች የፖለቲካ ኮንፈረንስ ላይ ተናግረዋል። በትላንትናው እለት ህሮማድስኬ ተብሎ የሚጠራዉ የዩክሬን የቴሌቭዥን ጣቢያ እንደዘገበው፤ ኪዬቭ በማዕድን ሀብቷ ዙርያ ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር ስምምነት ለማድረግ እንዳልተዘጋጀች የሚገልጹ የሚዲያ ዘገባዎችን ትክክለኝነት አረጋግጧል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia