የሱዳን ሉዓላዊ ምክር ቤት መሪ ከታጣቂዎች ጋር ድርድር እንደማይኖር ተናገሩ

የሱዳን ሉዓላዊ ምክር ቤት መሪ ከታጣቂዎች ጋር ድርድር እንደማይኖር ተናገሩ የሱዳን ሉዓላዊ ምክር ቤት ሊቀመንበር አብዱል ፋታህ አል-ቡርሀን፤ የክብር ነው ባሉት ጦርነት ከጦሩ ጎን ለተዋጉት፤ ጦራቸው የማያዋላዳ ድጋፉን ይሰጣል ማለታቸውን ሚዲያ ዘግቧል። ከካርቱም በምዕራብ አቅጣጫ በሚገኘው የኦምዱርማን የጦር ሰፈር ጉብኝት ባደረጉበት ወቅት ባደረጉት ንግግር፤ መጪው የሱዳን የፖለቲካ ምህዳር አካታች ይሆናል ብለዋል። "በሀገሪቱ የፖለቲካ ፕሮጀክት ላይ አጋሮች ይኖሩናል። ማንንም ከዚህ ውጭ አናደርግም" ማለታቸውን ጠቅሶ ሚዲያው ዘግቧል። የጦሩ አዛዡ ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ሙሉ ለሙሉ ከሀገሪቷ "እስኪነቀል" ድረስ፤ ወታደራዊ ተልዕኮው እንደሚቀጥል ቃል ገብተዋል። ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ የሱዳን ጦር በፈጥኖ ደራሹ ኃይል የበላይነቱን በመያዝ በካርቱም እና ሌሎች ክልሎች እየገሰገሰ ይገኛል ተብሏል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
Sputnik
የሱዳን ሉዓላዊ ምክር ቤት መሪ ከታጣቂዎች ጋር ድርድር እንደማይኖር ተናገሩ የሱዳን ሉዓላዊ ምክር ቤት ሊቀመንበር አብዱል ፋታህ አል-ቡርሀን፤ የክብር ነው ባሉት ጦርነት ከጦሩ ጎን ለተዋጉት፤ ጦራቸው የማያዋላዳ ድጋፉን ይሰጣል ማለታቸውን ሚዲያ ዘግቧል። ከካርቱም በምዕራብ አቅጣጫ በሚገኘው የኦምዱርማን የጦር ሰፈር ጉብኝት ባደረጉበት ወቅት ባደረጉት ንግግር፤ መጪው የሱዳን የፖለቲካ ምህዳር አካታች ይሆናል ብለዋል። "በሀገሪቱ የፖለቲካ ፕሮጀክት ላይ አጋሮች ይኖሩናል። ማንንም ከዚህ ውጭ አናደርግም" ማለታቸውን ጠቅሶ ሚዲያው ዘግቧል። የጦሩ አዛዡ ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ሙሉ ለሙሉ ከሀገሪቷ "እስኪነቀል" ድረስ፤ ወታደራዊ ተልዕኮው እንደሚቀጥል ቃል ገብተዋል። ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ የሱዳን ጦር በፈጥኖ ደራሹ ኃይል የበላይነቱን በመያዝ በካርቱም እና ሌሎች ክልሎች እየገሰገሰ ይገኛል ተብሏል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia