ግብፅ የእስራኤል እና የአሜሪካ ባለስልጣናት በጋዛ ሰርጥ ላይ የሰጡትን መግለጫ ውድቅ አድርጋለች ተባለ ካይሮ የትኛውም መፍትሄ የጋዛ ነዋሪዎች በመሬታቸው ላይ እንዲቆዩ ማስቻል አለበት ብላ ታምናለች ሲል አል-ቃሂራ የዜና አውታር ምንጮችን ጠቅሶ ዘግቧል። የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ዋሽንግተን ጋዛን መግዛት እንደማትፈልግ፤ ሆኖም ሰርጡን በቁጥጥሯ ሥር በማድረግ "በአግባቡ" እንደምታስተዳድር ማክሰኞ እለት ተናግረው ነበር። ባለፈው ሳምንት ጋዛን “ፍርስራሽ ቦታ” ሲሉ የገለጹት ትራምፕ፤ ዩናይትድ ስቴትስ መልሶ ግንባታውን "እንደምትረከብ" አስታውቀዋል። የጋዛ ሰርጥን ወደ “የመካከለኛው ምስራቅ የባህር ዳርቻ” ለመቀየር እና ፍልስጤማውያንን ግብፅ ወይም ዮርዳኖስ ወደመሳሰሉ ሀገራት በጅምላ ለማስፈር ማቀዳቸውንም ተናግረዋል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia