ቭላድሚር ፑቲን በናሚቢያ የመጀመሪያ ፕሬዝዳንት ሳም ኑጆማ ሞት የተሰማቸውን ሀዘን ለወቅቱ የሀገሪቱ መሪ ናንጎሎ ምቡምባ ገለፁ በክሬምሊን ድረ-ገጽ ላይ የታተመው መልዕክት "ሳም ኑጆማ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ግኑኝነት እንዲጎለበት ባደረጉት ጥረት ሩሲያ ውስጥ ይታወሳሉ፤ የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ ትብብሮችን ለማሳደግ ብዙ ሰርተዋል" ብሏል። ፑቲን በተጨማሪም የኑጆማ ስም "በዘመናዊው የናሚቢያ ታሪክ ውስጥ በጣም ወሳኝ ከሆኑት ክስተቶች ጋር በማይነጣጠል ሁኔታ የተቆራኘ ነው ሲሉ፤ የሀገሪቱን የነፃነት ትግል በመምራት እንዲሁም በናሚቢያ የመንግስሥት ተቋማት ግንባታ ያደረጉትን ትልቅ ግላዊ አስተዋፅኦ አንስተዋል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia