ኢትዮጵያ ካለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ400,000 ብልጫ ያለው 1.

ኢትዮጵያ የ1.34 ሚሊዩን ቶን የመዳበሪያ ግዢ ፈፀመች ፤ ይህ ቁጥር ካለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ400,000 ብልጫ አለው በማለት ሚኒስትሯ ተናገሩ የኢትዮጵያ መንግስት ቅድሚያ ከሚሰጣቸው ዘርፎች አንዱ የግብርና ዘርፍ ነው ፤ በዚህም ምክንያት ለገበሬዎች አስፈላጊ የሆነው የማዳበሪያ ምርት ያስገባው በማለት የግብርና ሚኒስትር ዲኤታዋ ሶፊያ ካሳ ተናግረዋል።ለ2017/18 የግብርና አመቶች የታቀደዉ 2.4 ሚሊዮን ቶን መዳበሪያ ሲሆን እስካሁን የተገኘው 1.35 ሚሊዩኑ ነው። ከዚህም መሀከል 640,000 ቶን ጅቡቲ ወደብ የደረሰ ሲሆን 400,000 ቶኑ ሀገር ውስጥ ገብቶ በመከፋፈል ላይ ይገኛል ተብሏል። ካሳ አክለውም ጅቡቲ ያለውን መዳበሪያ ለመጫን እየተደረገ ያለው ጥረት በጥሩ ሂደት ላይ ነው ብለዋል። የማዳበሪያው አከፋፈል እቅድም የሁሉንም የገበሬዎች ፍላጎት ተደራሽ ባደረገ መልኩ የሚደረግ ይሆናል ብለዋል። በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
Sputnik
ኢትዮጵያ ካለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ400,000 ብልጫ ያለው 1.34 ሚሊዮን ቶን የመዳበሪያ ግዢ ፈፀመች የኢትዮጵያ መንግሥት በግብርናው ዘርፍ ቀዳሚ ትኩረት ከሚሰጣቸው ጉዳዮች አንዱ ለአርሶ አደሩ አስፈላጊውን ማዳበሪያ ማቅረብ ነው ሲሉ የኢትዮጵያ የግብርና ሚኒስትር ደኤታ ሶፊያ ካሳ ተናግረዋል። በ2017/18 የምርት ዘመን 2.4 ሚሊየን ቶን ማዳበሪያ ለማግኘት የመነሻ እቅድ ተይዞ የነበረ ቢሆንም፤ 1.34 ሚሊየን ቶን ከወዲሁ መገኘቱን ሚኒስትሩ ጠቁመዋል። ከዚህ ውስጥ 640,000 ቶን ጅቡቲ ወደብ የደረሰ ሲሆን፤ በአሁኑ ወቅት ከ400,000 በላይ ቶን በመላ ሀገሪቱ እየተከፋፈለ እንደሚገኝ ገልጸዋል። አቅርቦቱን ከጅቡቲ ለማጓጓዝ እየተደረገ ያለው ጥረት በጥሩ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ሚኒስትሩ ጨምረው ጠቁመዋል። ክፍፍሉ የአርሶ አደሩን ፍላጎት በሚያሟላ መልኩ እንደሚከናወንም ነው ሚኒስትሩ የተናገሩት።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia