ኢትዮጵያ ካለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ400,000 ብልጫ ያለው 1.34 ሚሊዮን ቶን የመዳበሪያ ግዢ ፈፀመች የኢትዮጵያ መንግሥት በግብርናው ዘርፍ ቀዳሚ ትኩረት ከሚሰጣቸው ጉዳዮች አንዱ ለአርሶ አደሩ አስፈላጊውን ማዳበሪያ ማቅረብ ነው ሲሉ የኢትዮጵያ የግብርና ሚኒስትር ደኤታ ሶፊያ ካሳ ተናግረዋል። በ2017/18 የምርት ዘመን 2.4 ሚሊየን ቶን ማዳበሪያ ለማግኘት የመነሻ እቅድ ተይዞ የነበረ ቢሆንም፤ 1.34 ሚሊየን ቶን ከወዲሁ መገኘቱን ሚኒስትሩ ጠቁመዋል። ከዚህ ውስጥ 640,000 ቶን ጅቡቲ ወደብ የደረሰ ሲሆን፤ በአሁኑ ወቅት ከ400,000 በላይ ቶን በመላ ሀገሪቱ እየተከፋፈለ እንደሚገኝ ገልጸዋል። አቅርቦቱን ከጅቡቲ ለማጓጓዝ እየተደረገ ያለው ጥረት በጥሩ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ሚኒስትሩ ጨምረው ጠቁመዋል። ክፍፍሉ የአርሶ አደሩን ፍላጎት በሚያሟላ መልኩ እንደሚከናወንም ነው ሚኒስትሩ የተናገሩት።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia