ዋሽንግተን የጋዛን ነዋሪዎች ወደ ሞሮኮ እና ሶማሊያ ለማዘዋወር እያሰበች መሆኑን ሪፖርቶች አመለከቱ

ዋሽንግተን የጋዛን ነዋሪዎች ወደ ሞሮኮ እና ሶማሊያ ለማዘዋወር እያሰበች መሆኑን ሪፖርቶች አመለከቱ ዋይትሐውስ የጋዛ ነዋሪዎችን ሱማሊያ ውስጥ ራስ ገዝ ክልሎች ወደሆኑት እና ነፃነታቸውን ቢያውጁም በአለምአቀፍ ህብረተሰብ ዘንድ እውቅና ወዳልተሰጣቸው ሶማሌላንድ እና ፑትላንድ ለማዘዋወር እያሰበች ነው ፤ ሞሮኮም በተጨማሪ የጋዛ ነዋሪዎች እንዲዘዋወሩባት መታሰቡን የእስራኤሉ ኤን 12 የዜና ማሰራጫ ዘግቧል። ሁለቱ የሱማልያ ራስ ገዝ ክልሎች አለምአቀፍ እውቅናን ለማግኘት ፤ ሞሮኮ ከምእራብ ሰሀራዊት ጋር ያላትን የግዛት ይገባኛል ጥያቄ ለመፍታት ፤ ሶስቱም ከአሜሪካ የሚገኝ የፖለቲካ ጥቅምን እንደሚፈልጉ እና ሶስቱም ጋር ሱኒዎች በቁጥር አብላጫውን እንደሚይዙ ማሰራጫው ጨምሮ ዘግቧል።ዋሽንግተን የፈለገችው የጋዛ ነዋሪዎችን ለማጥፋት ሳይሆን ፤ የጋዛ ሰርጥን መልሶ ለመገንባት በሌሎች ተከበው ያሉትን የጋዛ ነዋሪዎች ከአደጋ ለማሸሽ ነው በማለት ማስረጫው አክሏል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
Sputnik
ዋሽንግተን የጋዛን ነዋሪዎች ወደ ሞሮኮ እና ሶማሊያ ለማዘዋወር እያሰበች መሆኑን ሪፖርቶች አመለከቱ ዋሽንግተን የጋዛ ነዋሪዎችን ሱማሊያ ውስጥ ራስ ገዝ ክልሎች ወደሆኑት እና ነፃነታቸውን ቢያውጁም በአለም አቀፍ ህብረተሰብ ዘንድ እውቅና ወዳልተሰጣቸው ሶማሌላንድ እና ፑትላንድ እንዳሁም ወደ ሞሮኮ ለማዘዋወር እያጤነች እንደሆነ የእስራኤሉ ኤን 12 የዜና ማሰራጫ ዘግቧል። ሁለቱ የሱማልያ ራስ ገዝ ክልሎች አለም አቀፍ እውቅናን ለማግኘት፤ ሞሮኮ በበኩሏ ምእራብ ሰሃራ ላይ ያላትን የግዛት ጥያቄ ለመፍታት የአሜሪካን የፖለቲካ ድጋፍ እንደሚፈልጉ እና ሶስቱም ጋር ሱኒዎች በቁጥር አብላጫውን እንደሚይዙ ማሰራጫው ጨምሮ ዘግቧል።የዋሽንግተን ጋዛን የማስለቀቅ እና መልሶ የመገንባት እቅድ ሰርጡን ወደ ነበረበት ለመመለስ እንጂ ዩናይትድ ስቴትስ ግዛቱን የመጠቅለል ዓላማ የላትም ሲል ዘገባው አክሏል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia