የጥር 26 ምሽት ዋና ዋና የዓለም ዜናዎች፦ 🟠 ከአውሮፓ ህብረት ባለስልጣናት ይልቅ ፑቲን ሁሌም የገቡትን ቃል ይጠብቃሉ ሲሉ የሀንጋሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ቪክቶር ኦርባን ተናገሩ። 🟠 ፊንላንድ በዩክሬን ቅጥረኛ ሆነው ለሚያገለግሉ የቆሰሉ ዜጎቿ የማስወጣት ወይም ህክምና የመስጠትን ጨምሮ ምንም አይነት እርዳታ እንደማታቀርብ የፊንላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሰነድ አመለከተ። 🟠 ቀኝ ዘመሙ አማራጭ የጀርመን ፓርቲ በምርጫ ፕሮግራሙ በሩሲያ ላይ የተጣለው ማዕቀብ በአስቸኳይ እንዲነሳ እና የኖርድ ስትሪም ማስተላለፊያ ወደነበረበት እንዲመለስ ጥሪ አቅርቧል ተባለ። 🟠 ሜክሲኮ ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር ያላትን ድንበር ለማጠናከር 10,000 ወታደሮችን እንደምታሰማራ የሜክሲኮ ፕሬዝዳንት ክላውዲያ ሼንቦም አስታወቁ። 🟠 የዩኤስ ኤድ ዋና መስሪያ ቤት ሰራተኞች ቢሮ እንደተዘጋ እና ወደ ስራ እንዳይመጡ የሚገልጽ ደብዳቤ እንደደረሳቸው የአሜሪካ መገናኛ ብዙሃን ዘገቡ። 🟠 ቻይና እ.አ.አ በ2026 በአስር ኪሎ ሜትሮች የሚዘል የምርምር መንኮራኩር ወደ ጨረቃ በመላክ በምድር ሳተላይት ደቡባዊ ዋልታ የውሃ አካል እንደምትፈልግ ተገለፀ።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia