ጋና የብድር ማሻሻያ ስምምነት ተፈራረመች ፤ ይህ ስምምነት በሀገሪቱ ያለውን ፋይናንስ ለማረጋጋት ከፍተኛ እርምጃ ነው ተብሏልበጋና የፋይናንስና ሚኒስቴር አማካኝነት ይፋ የሆነው የብድር ማገገሚያ ስምምነት ሀገሪቱ በጎርጎሮሳዊያን አቆጣጠር ከታህሳስ 2022 ጀምሮ የውጭ ብድርን አስለመልክቶ ያጋጠማትን ችግር ለመፍታት ወሳኝ እርምጃ ነው። አሁን ላይ የተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት በውስጡ በአለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይኤምኤፍ) የብድር ፕሮግራም አማካኝነት ከይፋዊ የብድር አቅራቢዎች ኮሚቴ ጋር የብድር - አገልግሎት እፎይታን ሀሳብን የያዘ ሲሆን ፤ በዚህም መሰረት ሁሉም አበዳሪ ሀገራት የጋናን የኢኮኖሚ እንዲያገግም በአንድነት እገዛ ያደርጋሉ።መሻሻሎች ቢታዩም ጋና አሁንም ከውጭ የንግድ አበዳሪዎች ጋር ያላትን ስምምነት አስተካክላ ለመጨረስ እየተደራደረች ነው። እነዚህ ውይይቶች ሁሉን አቀፍ ለሆነ እና ቀጣይነት ላለው የብድር አገልገሎት ወሳኝ ናቸው። የጋና ፋይናንስ ሚኒስቴር የተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት የሀገሪቱን ፋይናንስ ለማረጋጋት የጋራ ትብብር ውጤት እንደሆነና ለኢኮኖሚው መሻሻል መንገድ የሚከፍት፣ ለእድገት መነሳሳትን የሚፈጥር እና የኢንቨስተሮችን መተማመን የሚያድስ ነው ብሏል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia