የጥር 7 ምሽት አበይት የዓለም ዜናዎች፦⭕ ሩሲያ እና ዩክሬን 25 በ25 እስረኞችን መለዋወጣቸውን የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ።⭕ የሩሲያ ጦር ኃይሎች በግሎባል ፋይርፓዎር በዓመታዊ የዓለም ጦር ኃይሎች ደረጃ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀመጠ።⭕ የሩሲያ የኃይል ቀውስ ለገጠማት ትራንስኒስትሪያ ነዳጅ ጋዝን እንደ ሰብዓዊ እርዳታ ታቀርባለች ሲሉ የክልሉ መሪ የሆኑት ቫዲም ክራስኖሴልስኪ ገልጸዋል⭕ ከዚህ ቀደም ሚስጥራዊ ሰነዶችን በአግባቡ ባለማከማቸት የታወቁት የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን በድጋሚ ከዋይት ሃውስ በርካታ ሰነዶች በመውጣት ላይ መሆናቸውን የመገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል፤⭕ በኢስታንቡል በሐሰተኛ አልኮል በመመረዝ ሳቢያ ህይወታቸው ያለፈ ሰዎች ቁጥር ወደ 19 ከፍ ሲል በድምሩ 46 ሰዎች የህክምና እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው ተዘግቧል።⭕ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን በታላቁ የአርበኞች ጦርነት ድል 80ኛ ዓመት በዓል ለማክበር ዝግጅት የሚያደርግ አስተባባሪ ኮሚቴ ስብሰባን አካሂደዋል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia