የኒጀር ጦር በሀገሪቱ ምዕራባዊ ክፍል ባደረገው ተከታታይ ዘመቻ አንድ አሸባሪ መግደሉን እና ከአስር በላይ የሚሆኑትን በቁጥጥር ስር እንዳዋለ መገናኛ ብዙሃን ዘገቡ ለታጣቂዎች የሎጂስቲክስ መረብ ድጋፍ የሚሰጡ አራት ሕገ-ወጥ አዘዋዋሪዎችን በቁጥጥር ስር ከማዋል በተጨማሪ፤ የጸጥታ ኃይሎች በሞሲፓካ እና አዮሩ አካባቢዎች ድንገተኛ ወታደራዊ ጥቃት ማካሄዳቸውን መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። ኒያሚ ከሽብርተኝነት ጋር በተያያዘ በከባድ የጸጥታ ችግር እየተፈተነች ትገኛለች። ከቡርኪናፋሶ፣ ማሊ እና ናይጄሪያ ጋር በሚያዋስኑ የኒጀር አካባቢዎች ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ከፍተኛ የጽንፈኞች እና አሸባሪ ቡድኖች እንቅስቃሴ የጨመረ ሲሆን፤ ታጣቂዎች በወታደራዊ አባላት፣ የጸጥታ ኃይሎች እና በሰላማዊ ሰዎች ላይ ጥቃት ይሰነዝራሉ።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia