የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከጓዋንዡ አየር ማረፊያ "የቅርብ ትብብር ሽልማት" ተረከበ የጉዋንዡ ባዩን ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ፤ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር ላለው ጠንካራ አጋርነት እና ለአየር መንገዱ የአሰራር ብቃት እና አገልግሎት አሰጣጥ እውቅና ሰጥቷል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአሁኑ ወቅት ከጉዋንዡ ባዩን ዓለም አቀፍ አየር መንገድ በሳምንት 10 በረራዎችን የሚያከናውን ሲሆን፤ ይህም እንከን የለሽ የበረራ አገልግሎት ለመስጠት ቁርጠኛ እንደሆነ የሚያሳይ ነው ሲል የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘግቧል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ በማህበራዊ ትስስር ገጹ ባጋራው ጽሑፍ፤ ለጉዋንዡ ባዩን ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ የቀጠለ ድጋፍ ምስጋናውን ገለጾ፤ በቀጣይም ትብብራቸው ተጠናክሮ እንዲቀጥል ፍላጎቱ እንደሆነ ጠቁሟል። በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia