የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ከስፑትኒክ ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ያነሱት ዋና ነጥቦች በሩሲያ እና በአሜሪካ መካከል ስላለው ግንኙነት፤▫ ስትራቴጂካዊ የኑክሌር መሳሪያዎቿን በማዘመን ሩሲያ በስትራቴጂካዊ የጦር መሳሪያ ቅነሳ ስምምነት (ስታርት ስምምነት) ውስጥ የተቀመጡትን ገደቦች ሙሉ በሙሉ ማክበሯን ቀጥላለች።▫ ሩሲያ ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር በሚኖሯት የሚሳኤል እና የኑክሌር ግንኙነት ውስጥ ተቀባይነት ያለው የትንበያ ደረጃን ለመጠበቅ በርካታ እርምጃዎችን ተግባራዊ ማድረግ ለመቀጠል ዝግጁ ናት ።▫ ሩሲያ ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር ሊገመት የሚችል የኑክሌር ሚሳይል ግንኙነትን ለማረጋገጥ የተለያዩ እርምጃዎችን ለመውሰድ ፈቃደኛ ናት።▫ ዋሽንግተን የፀረ-ሩሲያ አቋሟን እስካልቀየረች ድረስ ሩሲያ ከአሜሪካ ጋር የጦር መሳሪያ ቁጥጥር ውይይት ላይ አትሳተፍም።▫ አሜሪካ እና ኔቶ ለሩሲያ አዲስ የሚሳይል ጉዳት ቢፈጥሩ ከሞስኮ በወታደራዊ-ቴክኒካል መልሶ ማጥቃት መልክ የኢምቢተኝነት አጸፋን ይቀበላሉ።▫ ሩሲያ የመካከለኛ እና የአጭር ርቀት የመሬት ሚሳኤሎችን በማሰማራት ላይ ያላትን የአንድ ወገን ጊዜያዊ እገዳ ትተዋለች፤ ይህም ዛሬ ተግባራዊ የማይሆን ቢሆንም ተጽዕኖው ግን ይኖራል።🪖የዩክሬንን ግጭት በተመለከተ፤▫ የዩክሬን ጦር ኃይሎችን ለማጠናከርና ዳግም ለማደራጀት የኬቭ አመለካከት እና ምዕራቡ ዓለም ውይይት ውጤታማ አይደለም፤ መፍትሄው ሊመጣ የሚችለው የሩሲያ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ያቀረቡትን ሀሳብ ተግባራዊ በማድረግ ብቻ ነው።▫ ሞስኮ በዩክሬን ዙሪያ ያለውን ሁኔታ ለመፍታት ለድርድር ዝግጁ ናት፤ ነገር ግን የቀውሱ መነሻዎችን ለማጥፋት እና "በመሬት ላይ ያለውን" እውነተኛ ሁኔታን ከግምት ውስጥ ማስገባት አለባቸው።▫ የዴንማርክ ሁለተኛው ምድብ F-16 ተዋጊ አውሮፕላኖችን ለኬቭ ማቅረባቸው የዩክሬንን ግጭት የበለጠ እንዲባባስ በማድረግ ሩሲያ ወታደራዊ-ቴክኒካዊ ባህሪ ያላቸውን ጨምሮ ተገቢ እርምጃዎችን እንድትወስድ አስገድዷታል። በሩሲያ እና ኢራን መሀከል የተፈረመውን የአጋርነት ስምምነት በተመለከተ ፤▫ ሩሲያ እና ኢራን አጋርነት ለተፈራረሙባቸው የፀጥታ ፣ የመከላከያ እና የፀረሽብርተኝነት ትብብሮች ያላቸውን ቁርጠኝነት በአዲስ ሰምምነት የሚያሳዩ ይሆናል።▫ በሩሲያ እና በኢራን መሀከል ያለው የእስትራቴጂክ አጋርነት ስምምነት ለፊርማ የተዘጋጀ እና በሶሪያ ያለው ሁኔታ በስምምነቱ ላይ ምንም አይነት ለውጥ አላመጣም። ▫ በሩሲያ እና በሞስኮ መሀከል የሚፈረመው አዲስ ስምምነት በሞስኮ እና በቴህራን መሀከል ያለውን ትብብር በተለይም በፀጥታ እና በመከላከያ ዘርፍ የማሳደግ ፍላጎት ያሳያል። በሶሪያ ያለውን ሁኔታ በተመለከተ▫ ሞስኮ በሶሪያ አዲስ ባለስልጣናት ፤ በሶሪያ ያላትን የጦር ሰፈር አስመልክቶ ያደረጉትን ማሻሻያ አለማወቋን እንዲሁም ይህንኑ አስመልክቶ ከደማስቆ የተላለፈላቸው ጥያቄ እንደሌለ ተናግረዋል።▫ በሶሪያ ያለውን የሩሲያ የጦር ሰፈር አስመልክቶ የስራ ሁኔታ እና የጥገና ጉዳዩችን አስመልክቶ ከአዲሱ አስተዳደር ጋር ድርድር ሊኖር ይችላል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia